የዞን ዘጠኝ ጉዳይ ለሰባተኛ ጊዜ ተቀጠረ

  • መለስካቸው አምሃ

ዞን-9

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በኢንተርቴት አምደኞቹ በእነ ሶሊያና ሽመልስና በአቃቤ ሕግ መካከል ባለው ክርክር ላይ ውሳኔ ለመስጠት መዝገቡን ለሰባተኛ ጊዜ ቀጠረ፡፡

ዛሬ ውሳኔ መስጠት ያልቻለው በጉዳዩ ውስብስብነት ሳቢያ እያንዳንዱ የችሎቱ ዳኛ እንዲመረምረው ሲባል ጊዜ በመውሰዱ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኛ ሰሚ ችሎት በአቤት ባይ አቃቢ ሕግና በመልስ ሰጪዎቹ የኢንተርኔት አምደኞቹ ሶሊያና ሽመለስ፣ በፍቃዱ ሃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፉ ብርሃኔ እና አቤል ዋበላ መካከል ባለው ክርክር ላይ ዛሬ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ከውሳኔ እንዳልደረሰ አስታወቀ፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የዞን ዘጠኝ ጉዳይ ለሰባተኛ ጊዜ ተቀጠረ