በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የፌድራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዛሬ ውሎና ክስ ያልተነሳላቸው የዞን ዘጠኝ አምደኞች ጉዳይ


ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:33 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የፌድራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ የወንጀል ችሎት ክስ ባልተነሳላቸው የዞን ዘጠኝ አምደኞች ጉዳይ ዛሬ ብይን ይሰጣል፤ ተብሎ ቢጠበቅም ለሌላ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል። ተከሳሾች የተለያዩ አቤቱታዎችን ለችሎቱ አቅርበዋል።

በሌላ ዜና በዚሁ ችሎት ብይን ከእስር እንዲፈቱ ባለፈው ሳምንት ትዕዛዝ የተሰጠላቸው የቀድሞው የአንድነት የአመራር አባል አቶ ሃብታሙ አያሌው እና ሰባተኛው ተከሳሽ አቶ አብረሃም ሰለሞን እስከ ዛሬም ከእስር አልተፈቱም።

የፍርድ ቤቱ ብይን በአቃቤ ሕግ የይግባኝ አቤቱታ መታገዱ ነው፤ የተነገረው። በጉዳዩ ላይ የሕግ አስተያየት ባለ ሞያዎች ግን እግዱ የሕግ መሠረት የለውም ይላሉ።

XS
SM
MD
LG