እነ አቶ ሃብታሙ አያሌው የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ ከችሎት እንዲነሡላቸው ጠይቀዋል።
በኦሮሚያ ክልል ሲደረጉ በቆዩ የተቀዉሞ ሰልፎች የተገደሉ ዜጎች ቁጥር ከ30 በላይ መድረሱን ዛሬ የኢትዮኢጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ገለጸ። የቆሰሉትና የታሰሩትም በመቶዎች እንደሚቆጠሩ አስታዉቋል።
የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተግባራዊ የሚሆነው ሕዝቡ ሲያምንበት ብቻ እንደሆነ ሁለት የመንግሥት ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ኢዴፓ ባወጣው መግለጫ በአሁኑ ጊዜ በሃገሪቱ በተለያዩ ክፍሎች የተነሱትን ችግሮች ለመፍታት መንግሥት የተከተለው መንገድ አሳስቦኛል አለ።
በኢትዮጵያ ሕፃናትን ለሥራ ማሠማራትና ጉልበት ብዝበዛን ለማስቆም የታቀደ ፕሮጀክት በተመረጡ ክልሎች ውስጥ ሊጀመር እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የቀድሞ አመራር አባል ሃብታሙ አያሌውና ሌሎች ተከሣሾች ጠበቃና አቃቤ ሕግ ሊያደርጉት የነበረው ክርክር ለሌላ ቀን ተቀጥሯል።
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ሰሞኑን በኦሮሚያ የተለያዩ ክፍሎችና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለተቀሰቀሰው ሁከት መንስዔ ነው ብሏል።
ኦሮሚያ ውስጥ እየታየ ላለው የተማሪዎች ተቃውሞና መዘዝ ተጠያቂው መንግሥት እንደሆነ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ - ኦፌኮ ክሥ አሰምቷል፡፡
የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት (UNHCR) ከኤርትራ ከሚመጡ ስደተኞች መካከል ከ81,000 በላይ የሚሆኑ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ገብተው እንደሚኖሩ ቢገመትም አድራሻዎቻቸው በትክክል እንደማይታወቅ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሣይንስ አካዳሚ ሁለተኛ ጉባዔ ዛሬ ተፈፅሟል።
የመረጃ ነፃነት የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መረጋገጥና ሌሎች መብቶች መከበር መሣሪያ እንደሆነ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ አሳስበዋል።
ዛሬ በአለማችን የሚገኙት የመጨረሻዎቹ አዳጊ ሀገሮች ለሚቀጥሉት 15 አመታት ድህነትን ከምድረ-ገጽ ፈጽሞ ለማጥፋት በሚደረገው ፍልሚያ ወሳኝ የትግሉ መድረክ እንደሚሆኑ ተገለጸ።
ፍርድ ቤት በነፃ ያሰናበታቸው የኢትዮጵያ ጦማርያንና ጋዜጠኞች፥ መከራና እንግልት እየተፈጸመባቸው መሆኑን በኢንተርኔት ባሠራጩት ዜና አስታወቁ።
በኢትዮጲያ በትራፊክ አደጋ ምክንያትከዓመት ዓመት የሚታየው የተጎጂዎች ቁጥር አሁንምእየጨመረ ነው ተባለ።
የአየር ንብረት ለውጥ በኢትዮጵያ ያለውን የጤና ችግር ሊያባብስ እንደሚችል የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ።
የኤል ኒኞ ክስተት ኢትዮጵያ ውስጥ ያስከተለው ድርቅ ከአንድ ዓመት በፊት ይታወቅ እንደነበር ተገልጿል፡፡
ለፌደራሉ መንግሥት አቤቱታውን እንድናቀርብ የኮንሶ ሕዝብ ወክሎ ልኮናል ያሉ ሰዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ፡፡
የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ-ሰሚ ችሎት በአምስቱን የተቃዋሚ መሪዎች ላይ ለቀረበዉ ከስ ለአራተኛ ጊዜ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ።
በሶማሌ ክልል ከ65 በላይ ሰዎች መገደላቸው የቀድሞው የኢትዮጲያ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ሰመጉ (HRCO) በ139ኛው ልዩ መግለጫው ላይ ይፋ አደረገ።
ተጨማሪ ይጫኑ