ታሊባኖቹ ዒላማ ያደረጉት በሀገሪቱ የስለላ ድርጅት ስር ያለ እና የመንግስት ባለስልጣናት ደህንነት ጥበቃ ኃይል መቀመጫ ሕንጻ መሆኑን ባለ ስልጣናቱ ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አደራዳሪነት በየመን ተፋላሚ ወገኖች መካከል ለሰኞ ተይዞ የነበረው የሰላም ድርድር ለሌላ ጊዜ መተላለፉ ተዘገበ። በኩዌት በዛሬው እለት ሊጀመር ታቅዶ የነበረው የመናዊ-ከየመናዊ የተባለው የሰላም ድርድር በየመን የመንግስታቱ ድርጅት ልዩ መልዕክተኛ ኢስማኢል ኦላድ ቼክ አህመድ ማብራሪያ፤ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በተከሰቱ ሁኔታዎች ሳቢያ ለሌላ ጊዜ ተላልፏል። የምክኒያቶቹን ተጨባጭ ምንነት ግን ልዩ መልዕክተኛው አልዘረዘሩም።
“ኢራቅ የምታካሂደው ዋና ፍልሚያ ሞሱል ላይ የሚካሄደው መሆኑን ሁሉም ያውቃል፤” ያሉት አንድ የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚንስቴር ከፍተኛ ባለ ሥልጣን፤ “ሞሱል ለኢራቅ ጦርነት የመጨረሻዋ የፍልሚያ ሜዳ ናት፤” ብለዋል የዩናይትድ ስቴትሱ የመከላከያ ሚንስትር አሽ ካርተር።
የብራዚል የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የ68 ዓመቱዋ ግራ ዘመም መሪ ከስልጣን እንዲሰናበቱ በመጪው ግንቦት ወር ድምጽ ሊሰጥ እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን፤ ይልቀቁ የሚል ውሳኔ ላይ ከተደረሰ የክስ ሂደቱ ባይጠናቀቅም ለስድስት ወር ያህል ስልጣን መልቀቅ ይኖርባቸዋል።
ድንበር ተሻግረው ጥቃቱን ያደረሱት የመሪሌ ጎሣ አባላት ናቸው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ከስሷል። ከመቶ በላይ ሕፃናት ተጠልፈው ተወስደዋል።
ይሁንና ምን ዓይነት አቀባበል እንደሚደረግላቸው እና መቼ ቃለ መሃላቸውን እንደሚፈጽሙ መንግስቱና ተቃዋሚዎቹ አሁንም ከስምምነት አልደረሱም።
ተቃዋሚዎቹ ጥያቄውን ያቀረቡት ትናንት ከብዙ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያ የሆነውን የተቃውሞ ሰልፍ ባካሄዱበት ወቅት ነው።
ሪፑብሊካኑ ሴኔተር ቦብ ኮርከር የመንግሥታቱ ድርጅት ሰላም አስከባሪዎች በተለይም በመካከለኛ አፍሪካ ሪፑብሊክና በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ የተመደቡት ወታደሮቹ ፈጸሙት የተባለው ወሲባዊ ጥቃት እጅግ ያስቆጣቸው መሆኑን አመልክተዋል።
የምስራቅዋ ጊሱሩ ከተማ ነዋሪዎች ሲናገሩ ሰባት ወንጀለኞች ገበያው ውስጥ እየሮጡ ከተኮሱ በኋላ አምልጠዋል ብለዋል።
አጥቂው ቦምቡን ያፈነዳው የየመኑ መንግስት በሳውዲ አረቢያ በሚመራው ህብረት ሃይሎች ርዳታ ሁቲዎቹን ተዋጊዎች አባርሮ መቀመጫው ባደረጋት ከተማ በተሰባሰቡ ምልምል ወታደሮች መሃል መሆኑ ታውቋል።
እኩለ ሌሊት ላይ በደረሱት ጥቃቶች ሶስት ሲቪሎች እና አምስት የጽንፈኛው ቡድን ተዋጊዎች መገደላቸውን የኪስማዮ ባለስልጣን እና የመንደሩዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ዩኒሴፍ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት ባለፈው እ.አ. አ. 2015 ዓ. ም. አርባ አራት ልጆች በቦኮ ሃራም አጥፍቶ ጠፊ ቦምብ ጥቃት መሳተፋቸውን ገልጾ ይህም ከዚያ በቀደመው ዓመት ከተሳተፉት አራት ልጆች ጋር ሲነጻጸር በአስር ዕጥፍ የሚበልጥ መሆኑን አመልክቷል።
የሲ አይ ኤ ዳይሬክተር በቀጣይ ፕሬዚደንት ቢታዘዝም እስረኞችን ውሃ ውስጥ የሰጠሙ እንዲመስላቸው በሚያደርገው የምርመራ ዘዴ እንደማይጠቀሙ ተናገሩ።
ዛሬም ብዛት ያላቸው ፍልሰተኞች በድንበር አጥሩ በግሪክ በኩል ተሰባስበዋል። ግጭት ስለመከሰቱ የተሰማ ዘገባ ግን የለም።
በየመን መንግስት፣ በሚደግፈው በሳውዲ የሚመራው ህብረት እና ከሁለት ዓመታት በፊት ዋና ከተማዋን ሰንዓን በተቆጣጠሩት በሁቲዎቹ አማጽያን መካከል ተኩስ አቁሙ የተጀመረው ዕኩለ ሌሊት ላይ መሆኑ የዛሬ ሳምንት ሰኞ ኩዌት ውስጥ ከሚጀመረው የየመን የሰላም ድርድር ታውቋል።
የተለያዩ የኤርትራውያን ተቃዋሚዎች ሬድዮዎችና ድረ-ገጾች ግን የሞቱት ወጣቶች ብዛት ከአራት እስከ 11 ነው ይላሉ።
የቡሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አላን ኒያሚትዌ መንግስታቸው በፀጥታ ሐይሎችና በደጋፊዎቹ አማካኝነት የተቃዋሚዎችን መብት ይጥሳል ተብሎ ከዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የቀረበውን ውንጀላ ውድቅ አድርገዋል።
በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች አካባቢ የነበረው ድባብ ሰላማዊ እንደነበር አንዳንዶቹ ድምጽ ሰጪዎች ሲናገሩ ብዛት ያለው ወታደር አይተናል ያሉም አሉ።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማርክ ቶነር ባወጡት መግለጫ በምርጫው ሂደት በስፋት የተዘባ አሰራር እንደታየበት ጠቅሰው የድምጽ አሰጣጡ በሰላማዊ መንገድ ተጀምሮ በኋላ የተቃዋሚ ደጋፊዎች መታሰራቸው ሂደቱን አጉድፎታል ብለዋል።
አለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ትናንት በሰጠው መግለጫ መሰረት ሮጀርዮ ዛንዳመላ የአስተዳደር ሁኔታን ማሻሳል፣ የገንዘብ አያያዝንና በገንዘባዊ ዘርፍ ልማት ማዳበር በሚመልከቱ ፖሊሲዎች ላያ አትኩረው ለመነጋገር በናይሮቢ ለሰባት ቀናት ያህል ከሶማልያ ባለስልጣኖች ጋር ተሰብስበዋል።
ተጨማሪ ይጫኑ