በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ታላቁ የኅዳሴ ግድብ Great Reninssance

የኅዳሴ ግድብ አንዱ ተርባይንን ሥራ መጀመርን በተመለከተ የተሰናዳ ዝግጅት

የኅዳሴ ግድብ አንዱ ተርባይንን ሥራ መጀመርን በተመለከተ የተሰናዳ ዝግጅት
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:00 0:00

ኢትዮጵያ ለአውሮፓ የኤሌክትሪክ ኃይል የማቅረብ ፍላጎት እንዳላት ትናንት የካቲት 13/2012 ዓ.ም የኅዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች አንዱን መርቀው ሥራ ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ።

አጠቃላይ ግንባታው ወደ መጠናቀቁ የተቃረበውና ውሃ የማቆሩን ሁለት ዙሮች በተሳካ ሁኔታ የጠናቀቀው የኅዳሴ ግድብ አንዱን ተርባይን ሥራ ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ግብጽ እና ሱዳን በግድቡ ላይ ያላቸውን አቋም በመቀየር ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ግብጽ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመሩን ተቃውማለች፡፡

ግብጽ ያሰማችውን ተቃውሞ ተንተርሶ የአሜሪካ ድምፅ ለትንታኔ የጋበዛቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስና የዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህርና የዓለም አቀፍ የውሃ ጉዳዮች አዋቂው ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ “በህዳሴ ግንባታም ሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በተከናወነው ሥራ የተጣሰ ምንም ዓይነት ሥምምነት የለም” ብለዋል።

የአባይና የኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ማነጋገሩን እንደቀጠለ ነው

የአባይና የኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ማነጋገሩን እንደቀጠለ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:38 0:00

በአባይ አጠቃቀምና በታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ጉዳይ የኢትዮጵያ አቋም “ግትርነት የበዛበት” እንደሆነ በመግለፅ የግብፅ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር፣ አምባሳደር ሞሃመድ ሂጋዚ ወቅሰዋል።

ታላቁ ኅዳሴ ግድብ 700 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ሊጀምር ነው

ፎቶ ፋይል፦ ታላቁ የኅዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል፦ ታላቁ የኅዳሴ ግድብ

ኢትዮጵያ እአአ 2022 ጀምሮ ከታላቁ የኅዳሴ ግድቧ በዓመት 700 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር አስታወቀች።

ይህም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት አቅሟን በ14 ከመቶ እንደሚያሳድግላት ዛሬ አንድ ከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣን መናገራቸውን ከናይሮቢ ሮይተርስ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ የኢኖቬስን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የአይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሚኒስትር ደኤታ ሁሪያ አሊ ማህዲ በድረ ገጽ በይነ መረብ በተካሄደ የአፍሪካ ቴክኖሎጂ ፌስቲቫል ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፣

"ኢትዮጵያ የተለያዩ የኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጄክቶች ትልቁ በሆነው በታላቁ ኅዳሴ ግድቧ እአአ ከሚቀጥለው 2022 ጀምራ 700 ሜጋ ዋት ማመንጨት ትጀምራለች" ብለዋል።

"በኅዳሴው ግድብ ጉዳይ ሁሉንም የሚያግባባ አቋም ላይ እንደምትሠራ አልጄሪያ ቃል ገብታልናለች" አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

የአረብ ሊግ ቀጣይ ሊቀመንበር ትሆናለች ተብላ የምትጠበቀው አልጄሪያ፤ ሊጉ በኅዳሴው ግድብ ዙሪያ ሁሉንም ወገን የሚያግባባ አቋም እንዲይዝ ኃላፊነቷን እንደምትወጣ መግለጿን ኢትዮጵያ አስታወቀች።

39ኛው የአፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መደበኛ ስብሰባ ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ ከስብሰባው ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከተለያዩ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

ከነዚህም አንዱ የአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲሆኑ፣ የአረብ ሊግ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ሁሉንም ወገን የሚያግባባ አቋም እንዲይዝ ሀገራቸው እንደምትሠራ ቃል መግባታቸውን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ከቱርክ የጦር መሳሪያዎችን ሸምታለች በሚል ግብጽ ጉዳዩ እንደሚያሰጋት መግጿን በተመለከተ ለተነሳላቸው ጥያቄ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና በሰጡት ምላሽ፣ "ኢትዮጵያ ነጻ ሀገር እንደመሆኗ ከማንም ጋር ማንኛውንም ዓይነት ግንኙነት የመፍጠር መብት አላት" ብለዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

"በኅዳሴው ግድብ ጉዳይ ሁሉንም የሚያግባባ አቋም ላይ እንደምትሠራ አልጄሪያ ቃል ገብታልናለች" አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:35 0:00


የፀጥታ ም/ቤቱን ፕሬዚዳንታዊ መግለጫ እንደማትቀበለው ኢትዮጵያ አስታወቀች

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

ከሕዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ አስገዳጅ ስምምነት ላይ እንዲደረስ የጸጥታው ምክር ቤት ያወጣውን ፕሬዚደንታዊ መግለጫ ኢትዮጵያ እንደማትቀበል አስታወቀች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ የጸጥታው ምክር ቤት ፕሬዚደንት መግለጫ በአብዛኛው ከኢትዮጵያ አቋም ጋር የሚጣጣም ቢሆንም አስገዳጅ ስምምነት የሚባል ነገር ኢትዮጵያ እንደማትቀበል ገልጸዋል፡፡

የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ትናንት በነበረው ስብሰባ ላይ፣ የወቅቱ የምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የሚደረገውን ድርድር ዳግም እንዲጀምሩ እና በሁሉም ወገን ተቀባይነት ያለው አስገዳጅ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጠይቀዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

የፀጥታ ም/ቤቱን ፕሬዚዳንታዊ መግለጫ እንደማትቀበለው ኢትዮጵያ አስታወቀች
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:12 0:00


ለታላቁ ኅዳሴ ግድብ ከ1 ቢሊዮን 260 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከዲያስፖራው ከ1 ቢሊዮን 260 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

ባለፉት አስር አመታት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከዲያስፖራው 1 ቢሊዮን 263 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ምክር ቤትን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዛሬ ዘግቧል፡፡

የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ አስር ዓመታት መቆጠሩን ዘገባው አመልክቶ እስካሁን ከከውጭና ከአገር ውስጥ እስከ ነሃሴ 30 ቀን 2013 15 ቢሊዮን 931 ሚሊዮን የሚጠጋ ገንዘብ መዋጣቱን አስታውቋል፡፡

የግድቡ ሁለት ተርባዮኖች በቅርብ ወራት ውስጥ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማመንጨት እንደሚጀምሩ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያና ቱርክ ስምምነቶች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የቱርክ ፕሬዚዳንት ራሲፕ ጣዪፕ ኤርዶኻን
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የቱርክ ፕሬዚዳንት ራሲፕ ጣዪፕ ኤርዶኻን

ኢትዮጵያና ቱርክ በወታደራዊና በውኃ ዘርፎች በትብብር መስራት መስማማታቸውን ለመንግሥቱ ቅርበት ያለው ፋና ብሮድካስቲንግ ማምሻውን ዘግቧል።

የወታደራዊ ዘርፍ ስምምነቱን ከቱርክ አቻቸው ጋር የተፈራረሙት የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር ቀነአ ያደታ መሆንቸውን የዜና አውታሩ አመልክቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለይፋ የሥራ ጉብኝት ቱርክ የሚገኙ ሲሆን የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት ራሲፕ ጣዪፕ ኤርዶኻን እንደተቀበሏቸው ተዘግቧል።

የኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት ስኬት ትንታኔና አስተያየት

የኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት ስኬት ትንታኔና አስተያየት
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:17 0:00

በኅዳሴ ሁለተኛ ሙሌት ላይ የኢትዮጵያዊያን ምሁራን አስተያየት

ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የፌስቡክ ገፅ ላይ በስክሪን ቅጂ የተወሰደ
ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የፌስቡክ ገፅ ላይ በስክሪን ቅጂ የተወሰደ

ዳሴ ግድብ ሁለተኛ ሙሌት የተጠናቀቀው በከባድ ፈተናዎች ውስጥ መሆኑንና “ኢትዮጵያ ለተፅዕኖዎች የማትንበረከክ አገር መሆኗን ያሳየ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ለቪኦኤ ያካፈሉ ምሁራን ተናግረዋል።የምራቅ አፍሪካን ዲፕሎማሲና ፖለቲካ የቀየረ ነው” ብለዋል።

አባይንና ኅዳሴ ግድብን በሚመለከት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ማተኮር ያለበት በአፍሪካ አህጉር፥ በቻይናና በሩሲያ መንግታት ላይ እንዲሆንም ምሁራኑ መክረዋል።

ግብፅ በዛ መቀጠሏ እንደማይቀር የገመቱት ምሁራን የአገር መከላከያ ይልና የደንነት ራዎችን ማጠናክርና ማዘመን እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኅዳሴ ግድብ ኃ መሙላት አባይገድቦ ለልማት ከማዋል አልፎ ገሪቱ ላይ የነበረውን ጥላቻና የሴራ ፖለቲካንም የሚገታ ነው” ብለዋል ምሁራኑ።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

በኅዳሴ ሁለተኛ ሙሌት ላይ የኢትዮጵያዊያን ምሁራን አስተያየት
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:40 0:00


“ዋነኛው ውጤት ኃይል አመንጭተን ለሕዝባችን ኤሌትሪክ ስናቀርብ ነው” ዶ/ር ስለሺ በቀለ

ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የፌስቡክ ገፅ ላይ በስክሪን ቅጂ የተወሰደ
ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የፌስቡክ ገፅ ላይ በስክሪን ቅጂ የተወሰደ

ሁለተኛው ዙር የሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ዛሬ ከቀትር በፊት ተጠናቋል። ግድቡ ሞልቶ ውሀው በአናቱ ላይ ሲፈስ በስፍራው ተገኝተው የተመለከቱት የኢትዮጵያ ውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣ ሁለተኛው ሙሌት መጠናቀቁ በሁለት ተርባይኖች ኃይል ለማመንጨት እንደሚያስችል ተናግረዋል። የክረምቱ ዝናብ ከፍተኛ መሆኑ ግድቡ በፍጥነት እንዲሞላ ማስቻሉንም የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ ከዚህ በኋላ እስከ ሦስት ወራት ባሉት ጊዜያት የሚኖረው ቀጣይ ሥራ ኃይል ማመንጨት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በንግግራቸውም “ሁለተኛው ሙሌት በሁለት ተርባይኖች ኃይል ለማመንጨት የሚያስፈልገንን የውሃ መጠን ሙሉ ለሙሉ መያዝ አስችሎናል። ይህ በራሱ ትልቅ ውጤት ቢሆንም ዋነኛው ውጤት ግን ኃይል አመንጭተን ለሕዝባችን ኤሌትሪክ ማቅረብ ነው። ስለዚህ በቅርብ ጊዜ የእርሱንም ብስራት አምጥተን የምናደርስ መሆኑን ለመግለፅ እወዳለሁ” ብለዋል።

ግድቡ እስካሁን ሊከሰት የሚችል የጎርፍ አደጋን ቢያስቀርም ከሙሌቱ በኋላ ባለው የክረምት ጊዜ በተለይ ሱዳን የጎርፍ አደጋ እንደሚያሰጋት አብራርተው፣ ሁለቱ የታችኛው ተፋሰስ ሃገራት ግድቡ እንደሚጠቅማቸው በመረዳት በመልካም ጉርብትና ለመኖር መዘጋጀት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡

በግድቡ ጉዳይ በሦስቱ ሀገራት መካከል ያለው አለመግባባት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን፣ የሁለተኛው ሙሌት መሳካት ኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ የበላይነት እንዲኖራት የሚያስችል እንደሆነ በርካታ የዘርፉ ምሑራን ይስማማሉ፡፡

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

“ዋነኛው ውጤት ኃይል አመንጭተን ለሕዝባችን ኤሌትሪክ ስናቀርብ ነው” ዶ/ር ስለሺ በቀለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:19 0:00


“ሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ከተጠናቀቀ፣ ግብጽና ሱዳን ፊታቸውን ወደ ትብብር ይመልሳሉ” - አምባሳደር ዲና ሙፍቲህ

 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

የተመድ የሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ወደ አፍሪካ ሕብረት እንዲመለስ በጸጥታው ምክር ቤት አባላት መወሰኑ ለኢትዮጵያ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ ሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ከተጠናቀቀ፣ ግብጽና ሱዳን ፊታቸውን ወደ ትብብር ይመልሳሉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አምባሳደር ዲና ከትግራይ ክልል ጋር በተያያዘ በሰጡት መግለጫ ደግሞ፣ ለሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ መፈቀዱን አስታውሰው፣ ነገር ግን ሁሉም አውሮፕላኖች ሲገቡም ይሁን ሲወጡ አዲስ አበባ ላይ እንደሚፈተሸ ተናግረዋል፡፡ ከተኩስ አቁም ስምምነት ጋር በተያያዘ፣ሕወሓት ያስቀመጣቸውን ቅድመ ሁኔታዎች “ሊሆኑ የማይችሉ” በማለት ተቀባይነት እንደሌላቸውም ጠቁመዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በጸጥታው ምክር ቤት የተካሔደው ስብሰባ ዋነኛው ነው፡፡ ሁሉም የጸጥታው ምክር ቤት አባላት የግድቡ ጉዳይ ወደ አፍሪካ ሕብረት እንዲመለስ መግለጻቸውንያነሱት አምባሳደር ዲና፣ ይህም ለኢትዮጵያ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

“ይህ አጀንዳ ትላንትና አሜሪካን ሃገር በፀጥታው ምክር ቤት እንዳልሆነ ሆኗል። አጀንዳው ከዚህ በኋላ በፀጥታው ምክር ቤት ሊታይ አይችልም ማለት ይቻላል። ዐሥራ አምስቱም ማለት ይቻላል የድምፅ ቃናቸው ይለያይ እንጂ ወደዛው እንዲወሰድ ወስነዋል። እኛ ይህንን ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ስኬትነው ብለን ነው የወሰነው። ምክኒያቱም የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ የሆኑቱንም ያልሆኑትም አባላት በተለያየ መልኩ በተናጥልም ሆነ በተወካዮቻቸው አማካኝነት ስናነጋግራቸው ነበር የቆየነው እንግዲህ የዚህን ውጤቱን አይታችሁታል።” ብለዋል።

በሂደት ላይ የሚገኘው ሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ከተጠናቀቀ፣ ግብጽና ሱዳን ፊታቸውን ወደ ትብብር ይመልሳሉ ያሉት ቃል አቀባዩ፣ ከዚህ በኋላ የግድቡን ጉዳይ ወደ ጸጥታው ምክር ቤት አይወስዱትም ብለዋል።፡፡

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ከሚገኙ የናይል ተፋሰስ ሃገራት አምባሳደሮች ጋር ባደረገው ውይይት የሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ወደ ተመድ የጸጥታው ምክር ቤት መሄዱ ትክክል እንዳልሆነ ከመግባባት ላይ መደረሱን እና የአረብ ሊግ ጉዳዩ ወደ ጸጥታው ምክር ቤት እንዲሄድ ማድረጉለአፍሪካ ሕብረት እና ለአፍሪካ ሃገራት ያለውን ንቀት እንደሚያመለክት አምባሳደሮቹ ማንሳታቸውንም ገልጸዋል፡፡

አምባሳደር ዲና ከትግራይ ክልል ጋር በተያያዘ በሰጡት መግለጫ ደግሞ፣ ለሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ መፈቀዱን አስታውሰው፣ ነገር ግን ሁሉም አውሮፕላኖች ሲገቡም ይሁን ሲወጡ አዲስ አበባ ላይ አርፈው ፍተሸ እንደሚደረግባቸው ተናግረዋል፡፡ ፍተሻውከአውሮፕላኖች በተጨማሪ መኪኖችን እና ግለሰቦችንም እንደሚጨምርም አክለው ገልጸዋል፡፡

ለሰብዓዊ እርዳታ አድራሾች ሙሉ ለሙሉ የበረራ ፍቃድ መሰጠቱን የተናገሩት አምባሳደር ዲና ሙፍቲህ ነገር ግን ለበረራው ፈቃድ የተሰጠው በአዲስ አበባ በኩል መሆኑን ጠቁመዋል። “እዚህ ደርሰው ከዚህ ነው ወደዚያ የሚሄዱት። ከዚያ ሲጨርሱም በዚህ ነው የሚያልፉት።” ያሉ ሲሆን ፤“ከአዲስ አበባ ሲሄዱም ሆነ ሲመለሱ ፍተሻ ይደረጋል። ይህ ደግሞ በየትኛውም ዓለም አቀፍ መመዘኛ የሚደረግ ነው።” ብለዋል።

ለሃገር ደህንነት ሲባል የትኛውንም ዓይነት መጓጓዣዎች መፈተሽ መብት መሆኑንም አክለዋል።

የፈረሰውን የተከዜ ድልድይ መልሶ የመገንባት ሥራም መጀመሩን አምባሳደር ዲና በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡

ከተኩስ አቁም ስምምነት ጋር በተያያዘ፣ የትግራይ መንግሥት ነኝ ያለው አካል ያስቀመጣቸውን ቅድመ ሁኔታዎች “ሊሆኑ የማይችሉ” በማለት ተቀባይነት እንደሌላቸውም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት የኤምባሲዎቹን ቁጥር እንደሚቀንስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ማንሳታቸውን ተከትሎ፣ ኤምባሲዎች እየተዘጉ ስለመሆናቸው በማሕበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ መረጃዎች ሐሰት መሆናቸውንም አምባሳደር ዲናገልጸዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማሻሻያ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን በመጠቆም በሂደት ሊታጠፉ የሚችሉ ኤምባሲዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ግን ጠቁመዋል፡፡

በተቀናጀ መንገድ ከሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን የመመለሱ ሥራ የቀጠለ ሲሆን፣ ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እስከትናንት ሐምሌ አንድ ድረስ 21 ሺህ 182 ዜጎች መመለሳቸውም ተገልጿል፡፡ አምባሳደር ዲና ባለፈው ሳምንት በሰጡት መግለጫ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸውም ዜጎች ከሳዑዲእንዲመለሱ በመደረግ ላይ መሆኑን አንስተው፣ “ይህም በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማብዛት የሚደረግ ነው” ማለታቸው ይታወሳል፡፡

“ሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ከተጠናቀቀ፣ ግብጽና ሱዳን ፊታቸውን ወደ ትብብር ይመልሳሉ” - አምባሳደር ዲና ሙፍቲህ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:04 0:00


በኅዳሴ ግድብ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት የተጀመረው ድርድር እንዲቀጥል የጸጥታው ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ

በኅዳሴ ግድብ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት የተጀመረው ድርድር እንዲቀጥል የጸጥታው ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:39 0:00

በኅዳሴ ግድብ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት የተጀመረው ድርድር እንዲቀጥል የጸጥታው ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ

የጸጥታው ምክር ቤት እንዲሰበሰብ የአረብ ሊግ፣ የግብጽ እና የሱዳንን ጥያቄ በማንገብ፣ የምክር ቤቱ ተለዋጭ አባል ቱኒዚያ ባቀረበችው ጥያቄ መሰረት ምክር ቤቱ ትናንት ባደረገው ስብሰባ በአፍሪካ ሕብረት የሚመራውን ድርድር ደግፏል፡፡

በዚህ ስብሰባ ላይ ግብጽ፣ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ለጸጥታው ምክር ቤት ስጋትና ጥያቄዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን የኅዳሴ ግድብ ለግብጽ የሕልውና ስጋት እንደሆነ ለምክር ቤቱ የገለጹት የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ፣ ግብጽ ይህን እንደማትታገስ እና የጸጥታው ምክር ቤትም እርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል፡፡

ከግብጽ ጋር ተመሳሳይ አቋም የምታራምደው ሱዳንም እንዲሁ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ማሪያም አል ሳዲቅ አል ማህዲ በኩል ባስተላለፈችው መልዕክት ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ ያለ ስምምነት ግድቡን እንዳትሞላ ያግዳት ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ/የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ
የኢትዮጵያ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ/የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ

የዓባይ ወይም የናይል ወንዝ የሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የጋራ ሀብት መሆኑንም የገለጹት የኢትዮጵያው ተወካይ የተገኙት የኢትዮጵያ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው የሱዳንና የግብጽ ፍላጎት ከግድቡ ጋር የተያያዠ ሳይሆን ኢትዮጵያ ውሃውን እንዳትጠቀም ማድረግእንደሆነ አብራርተው፣ ኢትዮጵያ ብትፈልግ እንኳን የዓባይን ውሃ አለመጠቀም እንደማትችል አንስተዋል፡፡

ወትሮውን የተለያየ አቋም በማንጸባረቅ የሚታወቁትን አሜሪካና ሩሲያን ጨምሮ ሁሉም የምክር ቤቱ ቋሚና ተለዋጭ አባላትም በኅዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለው ልዩነት በአፍሪካ ሕብረት መሪነት በሚካሔደው ድርድር እንዲፈታ አሳስበዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ሰላምና ጸጥታ በአፍሪካ በሚል ርዕስ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ፣ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ትናንት ሐምሌ 1/2013 ዓ.ም ሌሊት ላይ ስብሰባ አድርጓል፡፡ ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት በትግራይ ክልል ጉዳይ የተሰበሰበው ምክር ቤቱ፣ ትናንትያደረገው ስብሰባ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ሁለተኛው ነው፡፡

የኅዳሴ ግድብ ጉዳይ በጸጥታው ምክር ቤት እንዲታይ የአረብ ሊግ፣ የግብጽ እና የሱዳንን ጥያቄ በማንገብ፣ የምክር ቤቱ ተለዋጭ አባል ቱኒዚያ ባቀረበችው ጥያቄ መሰረት ነው ምክር ቤቱ ስብሰባ የተቀመጠው፡፡

ኢትዮጵያ የግድቡን ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጀመሯ ይፋ ከተደረገ ከቀናት በኋላ በተካሔደው በዚህ ስብሰባ ላይ ግብጽ፣ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ከግድቡ ጋር በተያያዘ ያላቸውን አቋም አንጸባርቀው ለጸጥታው ምክር ቤት ጥያቄዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡

የኅዳሴ ግድብ ለግብጽ የሕልውና ስጋት እንደሆነ ለምክር ቤቱ የገለጹት የሃገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ፣ ግድቡ ግብጽ የምታገኘውን የውሃ መጠን በመቀነስ ሃገሪቱን ለተለያዩ ችግሮች እንደሚዳርግ በማብራራት፣ ግብጽ ይህን አትታገስም ብለዋል፡፡ የጸጥታው ምክር ቤትም ግድቡ ለግብጽ የሕልውና ስጋት እንዳይሆን ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ/የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ
የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ/የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ

“የሕዳሴ ግድብ በግብጽ ላይ የተለያዪ የውሃ እጥረቶችን ያስከትላል፤ ንጹህ የመጠጥ ውሃን ይቀንሳል፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮች የመስኖ ውሃ እንዳያገኙ ሊያደርግ ይችላል፤ በሺዎች ሄክታሮች የሚቆጠሩ የእርሻ መሬቶችን ያወድማል፣ በረሃማነትን ያስፋፋል ሥነ ምህዳራዊ ሥርዓትንም ይጎዳል፣ ለአየር ንብረት ለውጥ ችግሮችም ተጋላጭነትን ይጨምራል።ይህ ግብጽ ልትታገሰው የማትችለው እና የማትታገሰው ሁኔታ ነው፡፡ ስለዚህ ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ በጸጥታው ምክር ቤት በኩል ይህን ክስተት የመከላከል እና ግድቡ ለግብጽ የሕልውና ስጋት እንዳይሆን የተቻለውን ሁሉ ማድረግየግድ ያስፈልገዋል፡፡”

ሦስቱ ሀገራት በስድስት ወራት ውስጥ አስገዳጅ (አሳሪ) ስምምነት ላይ እንዲደርሱ እና ኢትዮጵያ የጀመረችውን ሁለተኛውን የውሃ ሙሌት እንድታቆም የሚጠይቀውን በቱኒዚያ የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሐሳብ የጸጥታው ምክር ቤት እንዲያጸድቅም የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጠይቀዋል፡፡

ከግብጽ ጋር ተመሳሳይ አቋም የምታራምደው ሱዳንም እንዲሁ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ማሪያም አል ሳዲቅ አል ማህዲ በኩል ባስተላለፈችው መልዕክት ግድቡ ለሱዳንም ስጋት መሆኑን አንስታለች፡፡ በተለይ ከሕዳሴው ግድብ በታች የሚገኘው የሮሳሪየስ ግድብ አደጋ እንደተደቀነበት እናበሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሱዳናው ያንም የግብርና ሥራቸው እንደሚስተጓጎል የገለጹት ሚኒስትሯ፣ ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ ያለስምምነት ግድቡን እንዳትሞላ ያግዳት ዘንድ ጠይቀዋል፡፡

የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያም አል ሳዲቅ አል ማህዲ /የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያም አል ሳዲቅ አል ማህዲ /የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገፅ ላይ የተወሰደ ስክሪን ቅጂ

“ምክር ቤቱ ቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በማረጋገጥ ረገድ በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የሚካሔደው ድርድር እንዲቀጥል በማድረግ፣ በሕብረቱ ጥላ ስር ተደራዳሪዎች ድርድራቸውን እንዲጀምሩ በማድረግ፣ ከስምምነት ላይ እንዲደረስ ዓለማቀፍ አደራዳሪዎች እና ታዛቢዎች ድርድሩን እንዲያስኬዱ በማድረግ፣ ኢትዮጵያ ስምምነት ሳይደረስ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሱዳናውያን ላይ ስጋት ከሚደቅን ከማንኛውም የተናጥል እርምጃ እንድትታቀብ በማድረግ ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡” ብለዋል።

ኢትዮጵያን በመወከል ንግግር ያደረጉት የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣ በግድብ ጉዳይ የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ሲቀመጥ ይህ የመጀመሪያው መሆኑን ጠቅሰው፣ የሕዳሴው ግድብ ጉዳይ በምክር ቤቱ መታየቱን በጽኑ አውግዘዋል፡፡ የግድቡ ሁለተኛ ሙሌት በ2015ቱ የመርሆች ስምምነት መሰረት የሚካሔድ እና የግድቡ የግንባታ አካል መሆኑንም ዶ/ር ስለሺ ገልጸዋል፡፡

የዓባይ ወይም የናይል ወንዝ የሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የጋራ ሀብት መሆኑንም የገለጹት ዶ/ር ስለሺ የሱዳንና የግብጽ ፍላጎት ከግድቡ ጋር የተያያዠ ሳይሆን ኢትዮጵያ ውሃውን እንዳትጠቀም ማድረግ እንደሆነ አብራርተው፣ ኢትዮጵያ ብትፈልግ እንኳን የዓባይን ውሃ አለመጠቀም እንደማትችልአንስተዋል፡፡

ዶ/ር ስለሺ ስለዚሁ ሲያስረዱ፤ “የጎረቤቶቻችንን ስጋት ለመቅረፍ በጥሩ እምነት ተደጋጋሚ ጥረት ካደረግን በኋላ ተቃውሞአቸው በግድቡ ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን ኢትዮጵያ ምንም ውሃ እንዳትጠቀም ማድረግ እንደሆነ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ተገደናል፡፡ እውነታው ግን እኛ ሌላ አዋጭ አማራጭየሌለን መሆኑ ነው፡፡ እንደግብጽ እና ሱዳን ኢትዮጵያ በቂ የከርሰምድር ውሃ የላትም፤ የባሕር ውሃም የለንም፣ 70 በመቶ የሚሆነው የኔ ሀገር ውሃ በናይል ተፋሰስ የሚገኝ ነው፡፡

ብንፈልግ እና ብንሞክር እንኳን ናይልን አለመጠቀም አንችልም፡፡ ኢትዮጵያውያን የናይል ወንዝን መጠቀም ይችላሉ ወይስአይችሉም የሚለውን የጸጥታው ም/ቤት መመለስ ይጠበቅበታል፡፡ በኢትዮጵያውያን ስም ይሕን ምክር ቤት እና ዓለማቀፉን ማህበረሰብ፣ ኢትዮጵያውያን ከናይል መጠጣት ይችላሉን የሚለውን እንዲመልሱ እጠይቃለሁ፡፡ ማናችንም ሌሎች ሲጠጡ እየተጠማን መቀጠል የለብንም፡፡” ብለዋል።

በመሆኑም ም/ቤቱ የግድቡን ጉዳይ መመልከት የለበትም ያሉት ዶ/ር ስለሺ፣ ይህ ስብሰባ የጸጥታው ምክር ቤት በግድቡ ጉዳይ የሚያደርገው የመጨረሻው ስብሰባ እንዲሆን እና ጉዳዩን ወደ አፍሪካ ሕብረት እንዲመልስ ጠይቀዋል፡፡

ወትሮውን የተለያየ አቋም በማንጸባረቅ የሚታወቁትን አሜሪካና ሩሲያን ጨምሮ ሁሉም የምክር ቤቱ ቋሚና ተለዋጭ አባላትም በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለው ልዩነት በአፍሪካ ሕብረት መሪነት በሚካሔደው ድርድር እንዲፈታ አሳስበዋል፡፡

በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የሚደረገው ድርድር በአስቸኳይ እንዲቀጥል የጠየቁት በተመድ የአሜሪካ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ ግሪን ፊልድ፣ ተደራዳሪ ሀገራት ሂደቱን ከሚጎዳ እርምጃ እንዲታቀቡም ጠይቀዋል፡፡

“የግብጽ እና የሱዳን የውሃ ደህንነት እና የግድቡ አስተዳደር እና ደህንነት ስጋት ከኢትዮጵያ የልማት ፍላጎት ጋር መታረቅ ይችላሉ፡፡ ይህ የሚጀምረው ውጤታማ እና ተጨባጭ ድርድሮችን በማድረግ ነው፡፡ እነዚህ ድርድሮች በአፍሪካ ሕብረት መሪነት መካሔድ እና በአስቸኳይ መጀመር አለባቸው፡፡ ይህሂደት በ2015 በተደራዳሪዎች የተፈረመውን የመርሆች ስምምነት መጠቀም አለበት፡፡ ይህን አለመግባባት ለመፍታት የአፍሪካ ሕብረት ትክክለኛው ቦታ መሆኑን እናምናለን፡፡ ውጤታማ ስምምነት ላይ ለመድረስ አሜሪካ ፖለቲካዊ እና ቴክኒካዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነች፡፡”

ኢትዮጵያ ባትቀበልም ግብጽ እና ሱዳን ከአፍሪካ ሕብረት በተጨማሪ ተመድ፣ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሕብረትም በአደራዳሪነት እንዲሳተፉ በተደጋጋሚ ጠይቀዋል፡፡ አለመግባባቶችን ለመፍታት ግብጽ የኃይል እርምጃ ልትወስድ እንደምትችልም መግለጿ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ከአፍሪካ ሕብረትውጭ አደራዳሪዎችን ማብዛት ፋይዳ እንደሌለው የገለጹት በተመድ የሩሲያ አምባሳደር ቫሲሊ ኔቤንዚያ ኃይል ስለመጠቀም የሚሰጡ መግለጫዎችም እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡

“የቴክኒክ እና የሕግ ባለሙያዎቹን ጨምሮ የአፍሪካ ሕብረት በግድቡ ላይ ያለውን ልዩነት ለመፍታት የሚያደርገውን ተሳትፎ እናደንቃለን፡፡ ይህ አህጉራዊ ድርጅት የውሃውን ችግር የመፍታት አቅሙ ገና አልተሟጠጠም ብለን እናምናለን፡፡ በኮንጎ ሊቀመንበርነት የሚመራው ህብረቱ በዚህ መንገድጥረቱን እንዲያጠናክር እንጠይቃለን፡፡ በድርድሩ ላይ አደራዳሪዎችን እና ታዛቢዎችን ማብዛት ውጤት አያመጣም፡፡ ይሁንና በተደራዳሪዎቹ ፍላጎት ሊሳተፉ ይችላሉ፡፡ ችግሩን ለመፍታት ኃይልን ስለመጠቀም የሚገልጹ መግለጫዎች መቆም እና መከልከል አለባቸው፡፡”

ምንም እንኳን ቱኒዚያ ባቀረበችው ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የተባለ ነገር ባይኖርም፣ ሁሉም የጸጥታው ምክር ቤት አባላት በአፍሪካ ሕብረት የተጀመረው ድርድር እንዲቀጥል አሳስበው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

(ዘገባውን በድምፅ ለማድመጥ የተያያዘውን ፋይል ይጫኑ)

በኅዳሴ ግድብ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት የተጀመረው ድርድር እንዲቀጥል የጸጥታው ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:39 0:00


በኅዳሴ፣ በሱዳን አቢዬይ፣ በሳዑዲ ጉዳዮች የውጭ ጉዳይ

ፎቶ ፋይል፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
ፎቶ ፋይል፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

መንግሥት የመከላከያ ሰራዊቱን ከትግራይ ክልል ያስወጣበት ዋነኛው ምክንያት ኢትዮጵያ ለተጋረጡባት የውጭ ስጋቶች ጦሩን ለማዘጋጀት መሆኑን አስታወቀ።

ኢትዮጵያ በተለይ ከሕዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ውስጥ ጣልቃ ለመግባት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በሱዳን ጥያቄ መሰረት፣ ኢትዮጵያውያን ሰላም አስከባሪዎች ከአቢዬይ ግዛት መውጣት ካለባቸው ተገቢውን ዕውቅና እና ክብር አግኝተው መሆን እንዳለበት ኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት መግለጿንም ተናግረዋል፡፡

በአራት ቀናት ብቻ ከሳዑዲ ከ9ሺህ 900 በላይ ዜጎች መመለሳቸውን ጠቅሰው፣ ይህም በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

በኅዳሴ፣ በሱዳን አቢዬይ፣ በሳዑዲ ጉዳዮች የውጭ ጉዳይ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:40 0:00


ግብፅና ሱዳን ወደ ኅብረቱ ጠረጴዛ እንዲመለሱ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ፎቶ ፋይል፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
ፎቶ ፋይል፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

ሱዳን እና ግብጽ ወደ አፍሪካ ህብረት ድርድሩ እንዲመለሱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ምክር ቤት እንዲገፋፋ የኢትዮጵያ መንግሥት ለምክር ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ ጠይቋል።

በተጨማሪም የምዕራባውያን ሃገሮች አምባሳደሮች ያለፈውን ምርጫ አስመልክቶ ባወጣቱ መግለጫ ላይየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቋሙን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ የሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለቪኦኤ ገልጸዋል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ግብፅና ሱዳን ወደ ኅብረቱ ጠረጴዛ እንዲመለሱ ኢትዮጵያ ጠየቀች
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:14 0:00


ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG