No media source currently available
የኅዳሴ ግድብ ሁለተኛ ሙሌት የተጠናቀቀው በከባድ ፈተናዎች ውስጥ መሆኑንና “ኢትዮጵያ ለተፅዕኖዎች የማትንበረከክ አገር መሆኗን ያሳየ ነው” ሲሉ አስተያየታቸውን ለቪኦኤ ያካፈሉ ምሁራን ተናግረዋል። “የምሥራቅ አፍሪካን ዲፕሎማሲና ፖለቲካ የቀየረ ነው” ብለዋል። አባይንና ኅዳሴ ግድብን በሚመለከት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ማተኮር ያለበት በአፍሪካ አህጉር፥ በቻይናና በሩሲያ መንግሥታት ላይ እንዲሆንም ምሁራኑ መክረዋል።