ዋሺንግተን ዲሲ —
ኢትዮጵያና ቱርክ በወታደራዊና በውኃ ዘርፎች በትብብር መስራት መስማማታቸውን ለመንግሥቱ ቅርበት ያለው ፋና ብሮድካስቲንግ ማምሻውን ዘግቧል።
የወታደራዊ ዘርፍ ስምምነቱን ከቱርክ አቻቸው ጋር የተፈራረሙት የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር ቀነአ ያደታ መሆንቸውን የዜና አውታሩ አመልክቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለይፋ የሥራ ጉብኝት ቱርክ የሚገኙ ሲሆን የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት ራሲፕ ጣዪፕ ኤርዶኻን እንደተቀበሏቸው ተዘግቧል።