በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የናይጄሪያው ጽንፈኛ ቡድን ቦኮ ሃራም የቺቦክ ከተማ ልጃገረዶችን ጠልፈው ከወሰዱ ሁለት ዓመት ሞላ


په ويلچېر د هرات د نجونو د باسکټبال لوبډله
په ويلچېر د هرات د نجونو د باسکټبال لوبډله

ከዚያ ወዲህ ሃምሳ ሰባቱ ልጃገረዶች ከጠላፊዎቻቸው እጅ ያመለጡ ሲሆን ሁለት መቶ አስራ ዘጠኙ እስካሁን አልተገኙም። ቦኮ ሃራም ከሁለት መቶ በላይ ልጃገረዶችን በጠለፈ በሁለት ዓመቱ ብቅ ያለ አዲስ ቪዲዮ ለወላጆቻቸው በህይወት አሉ የሚያሰኝ ተስፋ ፈንጥቋል።

የናይጄሪያው ጽንፈኛ ቡድን ቦኮ ሃራም ተዋጊዎች በሀገሪቱ ሰሜን ምስራቃዊ ክፍል የምትገኘው ቺቦክ ከተማ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት ወርረው ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ተማሪዎችን ጠልፈው ከወሰዱ ሁለት ዓመት ሞላ።

ከዚያ ወዲህ ሃምሳ ሰባቱ ልጃገረዶች ከጠላፊዎቻቸው እጅ ያመለጡ ሲሆን ሁለት መቶ አስራ ዘጠኙ እስካሁን አልተገኙም።

ፋይል ፎቶ - ከቦኮ ሃራም ቪድዮ የተገኘ
ፋይል ፎቶ - ከቦኮ ሃራም ቪድዮ የተገኘ

አዲስ ቪዲዮ ለወላጆቻቸው በህይወት አሉ የሚያሰኝ ተስፋ ፈንጥቋል

የናይጄሪያው ጽንፈኛ ቡድን ቦኮ ሃራም ከሰሜን ምስራቋ ቺቦክ ከመንደር ከሁለት መቶ በላይ ልጃገረዶችን በጠለፈ በሁለት ዓመቱ ብቅ ያለ አዲስ ቪዲዮ ለወላጆቻቸው በህይወት አሉ የሚያሰኝ ተስፋ ፈንጥቋል።

VOA60 Africa - New Video Shows 15 'Chibok Girls' But Parents Wary
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:00 0:00

ከአራት ወራት በፊት የተቀረጸ ነው ተብሎ በወጣው ቪዲዮ ላይ ያሉትን አብዛኞቹ ልጆች የማውቃቸው ናቸው ሲሉ አንዲት ተጠላፊዎቹ የመንደራችን ልጆች ናቸው ሲሉ እንዲት እናት ተናግረዋል።

የቺቦክ ልጃገረዶች የተጠለፉበትን ሁለተኛ ዓመት መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ በዋና ከተማዋ አቡጃ በተካሄደው “ልጆቻችንን አምጡልን“ የተባለው እንቅስቃሴ በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኙት አስቴር ያኩቡ እንባ እየተናነቃቸው፣ "ትክክል ነው። ቪዲዮው ላይ ያሉት እነሱ ናቸው። ዕርግጥ ተለውጠዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት እንደዚህ አልነበሩም፣ አድገዋል። ግን እነሱ ናቸው።" ብለዋል።

የናይጄርያ ወታደሮች በቺቦክ ከተማ
የናይጄርያ ወታደሮች በቺቦክ ከተማ

ቦኮ ሃራም ከቺቦኩ አዳሪ ትምህርት ቤት ስለጠለፋቸው 219ኙ ልጃገረዶች ከተወሰዱበት ጊዜ አንስቶ የት እንዳሉ ሳይታወቅ የከረመ ሲሆን ትናንት የወጣውና በታህሳስ ወር የተቀረጸ ነው የተባለው ቪዲዮ አስራ አምስቱ ልጃገረዶች ይታዩበታል።

በቪዲዮው ልጃገረዶቹ ማንነቱ ባልታወቀ ሰው ለሚቀርብላቸው ጥያቄ በሃውሳና በኪባኩ ቋዋንቋዎች ስማቸውንና ከየት እንደተጠለፉ ሲናገሩ ይሰማሉ።

የሀገሪቱ የማስታወቂያና የባህል ሚኒስትር ላኢ ሞሃመድ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ በሲ ኤን ኤን (CNN) ቴሌቪዥን የወጣውን ቪዲዮ ጥርጣሬ አድሮባቸዋል። መንግስታቸው ልጆቹ ያሉት እዚህ ነው የሚሉ የተሳሳቱ ጥቆማዎች በተደጋጋሚ ደርሶታልናም ብለዋል።

የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ክሪስ ስታይን (Chris Stein) ቺቦክ ኢምባላላ ከተማ ከተጠለፉት ልጃገረዶች የአራቱን ወላጆች አነጋግሯል። ባልደረባችን ቆንጂት ታየ ያዘጋጀችውን ዝርዝር ለማዳመጥ፣ የድምጽ ፋይሉን ይጫኑ።

የናይጄሪያው ጽንፈኛ ቡድን ቦኮ ሃራም የቺቦክ ከተማ ልጃገረዶችን ጠልፈው ከወሰዱ ሁለት ዓመት ሞላ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:29 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG