በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሪያክ ማቻር ቃለ መሃላና የደቡብ ሱዳን አዲስ ምዕራፍ ጅማሮ


“ማቻር ወደ ጁባ በሚመለሱበት ሂደት ወቅት የታዩት እክሎች፤ በደም መፋሰሱ ሳቢያ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያጠላው፥ እርስ-በእርስ በከፍተኛ ጥርጣሬ የመተያየትና ያለመተማመን ግዙፍ ችግር ማሳያ መሆኑን ሁሉም በግልጽ ይረዳል።” ሰማንታ ፓወር በተባበሩት መንግስታት የዩናይትድ ስቴትሷ አምባሳደር።

የደቡብ ሱዳኑ አማጽያን መሪ ሪያክ ማቻር ለዚያች አገር አዲስ ምዕራፍ ጅማሮ በታለመ ዕቅድ ትላንት ጁባ ላይ ዳግም የአገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ያደረጋቸውን ቃለ መሃላ ፈጸሙ።

ይሁንና በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው እርስ-በእርስ ያለመተማመን በቀጣዩ የሽግግር ወቅት ላይ እንዳያጠላ ሥጋት አሳድሯል። ጂል ክሬግ ከናይሮቢ ያጠናቀረችው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል። አሉላ ከበደ ያቀርበዋል።

ከረዥም ጥበቃ በኃላ በመጨረሻው ትላንት ከጁባ የአውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ሞቅ ያለ አቀባበል የጠበቃቸው የቀድሞው የደቡብ ሱዳኑ አማጽያን መሪ አዲሱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪያክ ማቻር ከተቀናቃኛቸው ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ጋር አዲስ የጋራ መንግስት ለመመስረት ነው የተመለሱት። ዝርዝሩን ከዚህ ያድምጡ፤

የሪያክ ማቻር ቃለ መሃላና የደቡብ ሱዳን አዲስ ምዕራፍ ጅማሮ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:16 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG