በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ታላቁ የኅዳሴ ግድብ Great Reninssance

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተጨማሪ ሁለት ተርባይኖች ኀይል ማመንጨት ጀመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለት ተርባይኖች፣ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ኀይል ማመንጨት መጀመራቸውን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናግረዋል፡፡

እያንዳንዱ ተርባይን 400 ሜጋ ዋት ኀይል እንደሚያመነጭ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በጥቂት ወራት ውስጥ ሦስት ተጨማሪ ተርባይኖች ሥራ እንደሚጀምሩም ጠቁመዋል፡፡

የግድቡ ግንባታ ወደ መጠናቀቅ እያመራ ስለመኾኑ እየተገለጸ ያለው፣ ከታችኞቹ የተፋሰሱ አገራት የሚነሡ ስጋቶች እና ተቃውሞዎች በቀጠሉበት ወቅት ነው፡፡

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተጨማሪ ሁለት ተርባይኖች ኀይል ማመንጨት ጀመሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:43 0:00

ደቡብ ሱዳን የናይል ተፋሰስ የትብብር ማኅቀፍ ስምምነትን ማጽደቋን ኢትዮጵያ አደነቀች

 ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ

ደቡብ ሱዳን፣ የናይል ተፋሰስ ባለፈው ሳምንት አጽድቃለች፡፡ ዐዲሷ የተፋሰሱ ሀገር የወሰደችውን ርምጃ፣ የጎረቤቷ ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ “ታሪካዊ” ሲሉ አድንቀዋል፡፡

በሌላ መጠሪያው “የኢንቴቤ ስምምነት” እየተባለ የሚታወቀው የናይል ተፋሰስ የትብብር ማኅቀፍ ስምምነት፣ በደቡብ ሱዳን መጽደቁ፣ ስምምነቱ በተፋሰሱ ሀገራት ተግባራዊ ሊኾን የሚችልበትን በቂ ድጋፍ የሚያስገኝ ነው፡፡

በዐዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሃይድሮ ፖለቲክስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር ኾና የትብብር ማኅቀፍ ስምምነቱን መፈረሟ፣ ስምምነቱ “ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝና ወደ ተግባር እንዲሸጋገር የሚያስችል ነው፤” ብለዋል፡፡

ዐሥራ አንዱም የተፋሰሱ ሀገራት የሚጋሩትን የናይል ወንዝ፣ “ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ለግብጽ እና ለሱዳን ብቻ ያከፋፍላሉ፤” በሚል የሚተቹትን የቅኝ ግዛት ስምምነቶች በመሻር በዐዲስ ለመተካት ታስቦ የተዘጋጀ መኾኑን ተመራማሪው ገልጸዋል፡፡

የትብብር ማኅቀፍ ስምምነቱ ሐሳብ አመንጪዎች እና ግንባር ቀደም ተዋናዮች ከኾኑት ሰባት የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት አንዷ የኾነችው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ “የናይል ወንዝ ተፋሰስ የትብብር ማኅቀፍ ስምምነት በደቡብ ሱዳን መጽደቁ ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ነው፤” ሲሉ፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ሐምሌ 10 ቀን 2016 ዓ.ም. በማኅበራዊ የትስስር ገጾቻቸው አወድሰዋል፡፡

የናይል ወንዝ ተፋሰስ የትብብር ማኅቀፍ ስምምነት በደቡብ ሱዳን መጽደቁ ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ነው፤”

ስምምነቱ ለ11 ዓመታት ከዘለቀ ውይይት በኋላ፣ በ2002 ዓ.ም. (በአውሮፓውያኑ 2010) ግንቦት ወር ላይ በኢትዮጵያ፣ ታንዛኒያ፣ ዑጋንዳ፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ሲፈረም፣ ብሩንዲ በቀጣዩ ዓመት ስድስተኛ ሀገር ኾና ፈርማለች፡፡ ከእነዚኽ ሀገራት መካከል ከኬንያ በቀር አምስቱ ስምምነቱን በየአገሮቻቸው ሲያጸድቁ፣ ደቡብ ሱዳን ስድስተኛዋ የስምምነቱ አጽዳቂ ሀገር ኾናለች፡፡

የናይል ተፋሰስ የውኃ ምንጭ የኾኑት የላይኛው የተፋሰሱ ሀገራት፣ የትብብር ማኅቀፍ ስምምነቱ፥ “ፍትሐዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም” የሚለውን መርሕ የሚያሟላ መኾን እንዳለበት ይገልጻሉ፡፡ ስምምነቱ፥ “የውኃ ደኅንነታችንንና ታሪካዊ ድርሻችንን ማረጋገጥ አለበት፤” የሚል አቋም ያላቸው ግብጽ እና ሱዳን በበኩላቸው፣ እስከ አሁን ስምምነቱን አልፈረሙም፡፡

ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር በመኾን ስምምነቱን ማጽደቋን ተከትሎ፣ ከሁለቱ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት እስከ አሁን በይፋ የተሰጠ መግለጫ የለም፡፡

ስምምነቱ በደቡብ ሱዳን መጽደቁን፣ “ዲፕሎማሲያዊ እመርታ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በበኩላቸው፣ ይህም “በናይል ተፋሰስ ቀጣናዊ ትብብር ለማድረግ ባለን የጋራ ምኞት ጉልሕ ርምጃ ነው፤” ብለዋል።

ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየታቸውን የሰጡት በዐዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሃይድሮ ፖለቲክስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፣ የደቡብ ሱዳን ውሳኔ፣ ከ11ዱ የተፋሰሱ ሀገራት ውስጥ የስምምነቱን አጽዳቂዎች ቁጥር ወደ ስድስት በማድረስ ወደ ተፈጻሚነት እንደሚያሸጋግረው ተናግረዋል፡፡ ይህም፣ ግብጽ እና ሱዳን፣ በቅኝ ግዛት ስምምነቶች መሠረት አለን የሚሉትን ታሪካዊ የውኃ መብት ጥያቄ የሚያስቀር እንደኾነ ያስረዳሉ፡፡

በአውሮፓውያኑ 1929፣ በግብጽ እና በብሪታኒያ መካከል የተፈረመው ስምምነት፣ ከቅኝ ግዛት ስምምነቶች አንዱ ነው፡፡ በናይል(ዓባይ) ወንዝ እና በተፋሰሶቹ ላይ የሚገነቡ ማንኛውም ግንባታዎች፣ “ያለግብጽ ይኹንታ እንደማይከናወኑ ይደነግጋል፤” ይላሉ ፕር. ያዕቆብ።

ደቡብ ሱዳን የናይል ተፋሰስ የትብብር ማኅቀፍ ስምምነትን ማጽደቋን ኢትዮጵያ አደነቀች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:34 0:00

የትብብር ማኅቀፍ ስምምነቱ በአንጻሩ፣ የናይል ተፋሰስ ሀገራት እያንዳንዳቸው በየግዛታቸው ውስጥ የናይል ወንዝን ውኃ ፍትሐዊ እና ምክንያታዊ በኾነ መንገድ የመጠቀም መብት እንዳላቸው ይገልጻል፡፡ ስምምነቱ፣ በስድስት ሀገራት

በተፈረመባቸውና በአምስቱ ከጸደቀ በኋላ ባሉ የተለያዩ ጊዜያት የግብጽ ባለሥልጣናት በሰጧቸው አስተያየቶች፣ ምንም እንኳን አገሪቱ የስምምነቱን በርካታ አንቀጾች ብትቀበልም፣ “ለአወዛጋቢ ጉዳዮች እልባት የሚሰጥ አይደለም በማለት” በተቃውሞዋ መቀጠሏን ገልጸዋል፡፡

ይኹን እንጂ፣ ስምምነቱ በስድስት ሀገራት መፈረሙን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መኾኑን የሚገልጹት የሃይድሮ ፖለቲክስ ተመራማሪ ፕር. ያዕቆብ አርሳኖ፣ ግብጽ እና ሱዳን አለመፈረማቸው ወደ ኋላ ሊመልሰው እንደማይችል ተናግረዋል፡፡

በስምምነቱ መሠረት፣ አባል ሀገራት፣ በናይል ተፋሰስ ውኃ ላይ በሚሠሯቸው ግንባታዎች ምክንያት ቅሬታዎች ቢነሡ፣ ስምምነቱ መጽደቁን ተከትሎ በሚቋቋም የናይል ተፋሰስ ኮሚሽን እልባት እንደሚሰጠውም አስረድተዋል፡፡

በትብብር ማኅቀፉ ስምምነት ላይ፣ በላይኛው የተፋሰሱ ሰባት ሀገራት እና በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ግብጽ እና ሱዳን መካከል መግባባት ካልተደረሰባቸው ነጥቦች መካከል፣ “በሌሎች የናይል ተፋሰስ ሀገራት የውኃ ደኅንነት ላይ ጉልሕ ተጽእኖ አለማሳደር” የሚለው አንቀጽ 14(ለ) ዋናው ነው፡፡

ይህ አንቀጽ “በሌሎች የተፋሰስ ሀገራት የውኃ ደኅንነት፣ እንዲሁም የአሁን አጠቃቀምና መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳያሳድር” በሚል እንዲተካ ግብጽ ጥያቄ አቅርባ ነበር፡፡

የናይል የሚኒስትሮች ምክር ቤት በግንቦት ወር 2001 ዓ.ም. በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኪንሻሳ ባካሔደው አስቸኳይ ስብሰባ፣ በአንቀጽ 14(ለ) ላይ የተመለከተው ጉዳይ፣ በናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን እልባት እንዲሰጠው ወስኗል፡፡

የናይል ወንዝ በውድቅዳቂ ቆሻሻ ተሞልቷል

የቆሻሻ መጣያ እና ውድቅዳቂ በአባይ ወንዝ ላይ ቦር፣ ጆንግሌይ ግዛት፣ ደቡብ ሱዳን
የቆሻሻ መጣያ እና ውድቅዳቂ በአባይ ወንዝ ላይ ቦር፣ ጆንግሌይ ግዛት፣ ደቡብ ሱዳን

በአህጉሪቱ ረዥሙ መሆኑ የሚነገርለት እና አሥራ አንድ አገሮችን አቋርጦ የሚፈሰው የናይል ወንዝ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥሩ ከ200 ሚሊዮን በላይ ለሚደርስ ሕዝብ ዘላቂ የሕይወት ዋስትና ይሰጣል። ይሁን እንጂ ከወንዙ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች የሚታየው እና እያደርም እየጨመረ የመጣው የሰዎች እንቅስቃሴ የወንዙን ሥነ-ምህዳር ለአደጋ ማጋለጡ ተዘግቧል።

የናይል ወንዝ በውድቅዳቂ ቆሻሻ ተሞልቷል
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:16 0:00

ሺላ ፖኒ ከደቡብ ሱዳኗ ጆንግሌይ ግዛት ቦር ያደረሰችንን የዚህን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ያለስምምነት በተጠናቀቀው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ግብጽ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌላት ተገለጸ

ያለስምምነት በተጠናቀቀው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ግብጽ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌላት ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:53 0:00

በዐዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ቀናት የተካሔደው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛው ዙር ድርድር፣ ያለስምምነት እንደተጠናቀቀ፣ ትላንት ያስታወቁት ኢትዮጵያ እና ግብጽ፣ ለውጤት አልባነቱ አንዳቸው ሌላቸውን ወንጅለዋል፡፡

ግብጽ፥ “ውይይቱ ያልተሳካው ኢትዮጵያ ምንም ዐይነት ስምምነት ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመኾኗ ነው፤” ስትል፤ ኢትዮጵያም በበኩሏ፣ “የስምምነቱን መንገድ የዘጋችው ግብጽ ናት፤” ብላለች፡፡

በድርቅ ወቅት የሚኖረው የውኃ አያያዝ እና አለቃቀቅ፣ በድርድሩ ከፍተኛ ልዩነት የታየበት ጉዳይ እንደነበረ፣ የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ዶር. ስለሺ በቀለ ገልጸዋል፡፡

ግብጽ፣ “ከዚኽ በኋላ ድርድሩን የመቀጠል ፍላጎት የለኝም፤” እንዳለች የገለጹት አምባሳደር ስለሺ፣ የአፍሪካ ኅብረት ዳግም ወደ አደራዳሪነቱ ሊመለስ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን፣ በዐዲስ አበባ ለሦስት ቀናት ያካሔዱት የታላቁ የሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ድርድር፣ ትላንት ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ያለስምምነት መቋጨቱን ያስታወቁት ኢትዮጵያ እና ግብጽ፣ ለውጤት አልቦነቱ እርስ በርስ ተወነጃጅለዋል፡፡

ያለፉት አራት ዙር ድርድሮች የተካሔዱት፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤል-ሲሲ፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት እና አለቃቅ ዓመታዊ ክዋኔ ላይ፣ በአራት ወራት ውስጥ የመጨረሻ ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ በ2015 ዓ.ም. ሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ በተስማሙት መሠረት ነው፡፡

ይኹንና፣ በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ሥር ሲካሔድ የቆየው የግድቡ ድርድር፣ በሚያዚያ ወር 2013 ዓ.ም ላይ ከተቋረጠ በኋላ፣ በሦስቱ የተፋሰሱ ሀገራት መካከል፣ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ፣ በካይሮ እና በዐዲስ አበባ በተደረጉ የአራት ዙር ድርድሮች ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም፡፡

ለድርድሮቹ ፍሬያማ አለመኾን፣ ኹለቱ ሀገራት ባወጡት መግለጫ እርስ በርስ ተወቃቅሰዋል፡፡

የግብጽ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር፣ “ውይይቱ ያልተሳካው፥ ኢትዮጵያ ምንም ዐይነት ስምምነት ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመኾኗ ነው፤” ሲል ከሷል፡፡

ስምምነት ላይ ላለመደረሱ፣ ግብጽን ተጠያቂ የምታደርገው ኢትዮጵያም፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችው መግለጫ፣ “ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን አስተሳሰቧ በመቀጠል፣ ወደ መግባባት የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች፤” ስትል ወቅሳለች።

የሦስትዮሽ ድርድሩ ሲካሔድ የነበረው፣ 16 አንቀጾች ባሉት የጋራ መደራደሪያ ሰነድ ላይ በመመሥረት ሲኾን፣ ከፍተኛ ልዩነት የታየውም፣ በድርቅ ወቅት በሚኖረው የውኃ አያያዝ እና አለቃቀቅ ላይ ትኩረት በአደረገው አንቀጽ እንደኾነ፣ የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ስለሺ በቀለ (ዶር.) ድርድሩን አስመልክተው፣ ዛሬ ረቡዕ፣ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

ልናስኬድ የቻልነው እስከ ስድስተኛው ክፍል ነው ነው። ስድስተኛው ክፍል ላይ ደግሞ ልዩነት አለ፡፡ ይሄም የድርቅ ሁኔታን የሚያመላክተው የውሃ አያያዝና አለቃቅ ጉዳይ ነው፡፡”

“ልናስኬድ የቻልነው እስከ ስድስተኛው ክፍል ነው ነው። ስድስተኛው ክፍል ላይ ደግሞ ልዩነት አለ፡፡ ይሄም የድርቅ ሁኔታን የሚያመላክተው የውሃ አያያዝና አለቃቅ ጉዳይ ነው፡፡” ያሉት ዶር. ስለሺ በዚህ ላይ መግባባትና መቀራረብ ስላልተቻለ፣ ስድስት ሰዎች ያሉበት የባለሞያዎች ቡድን ጉዳዩን እንደገና እንዲመለከት ሁለት ሰዎች መወከላቸውን ተናግረዋል። ከኢትዮጵያ የተወከሉት ሰዎች ደግሞ ከሁለቱ ቀናት የሚኒስትሮቹ ስብሰባ አንድ ቀን ቀደም ብሎ መወያየታቸውን አምባሳደር ስለሺ ጨምረው አስረድተዋል።

ድርቅ በሚያጋጥምበት ወቅት በሚለቀቀው የውኃ መጠን ላይ፣ በተደራዳሪዎቹ ሀገራት መካከል የቁጥር ልዩነቶች መኖራቸውን፣ አምባሳደር ስለሺ ጠቅሰዋል፡፡ በውኃው የክፍፍል መጠን ላይ ስምምነት በሌለበት ኹኔታ፣ ከታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት በተቃራኒ ኢትዮጵያ፣ ቋሚ ቁጥር መቀመጥ የለበትም፤ የሚል አቋም እንዳላት፣ ዋና ተደራዳሪው አብራርተዋል፡፡

“ይሔን ቁጥር ስንሰጥ የኢትዮጵያን የወደፊት የመልማት ዕድል በሚገድብ መልኩ ሳይኾንን፣ የትብብር ስለሆነ ያንን ሊያስተካክል የሚችለው ሁላችንም የውሃ መብት ክፍፍላችን ሲታወቅ በዛ ስሜት እንሠራ።አን። እስከዛው መረጃ እየተለዋወጥን መቀጠል አለብን የሚል አቋም ነው ያለን፡፡ ይሔ ደግሞ ፍትሐዊነት ነው፡፡ ሕዳሴ ግድብን ብቻ ስለሠራን ልማት አናቆምም፡፡ ከላይ የምንሠራቸው ግድቦች የውሃ ጉዳይ በኛ ድርሻ ውስጥ የሚካተት ነው፡፡ አሁን ያ ድርሻ የተቀመጠ ስላልሆነ በድርድር ውስጥ ለዚህ ዓይነት ችግር አጋልጦናል” ያሉት አምባሳደር ስለሺ ኢትዮጵያ፣ “ግትር አቋም ይዛለች፤” በሚል ግብጽ የምታቀርበውን ውንጀላም አስተባብለዋል፡፡

“ድርቅ ቢከሰት፣ ተፈጥሮ ከምትሰጠው በላይ ውሃ ጨምሮ ከመስጠት ሌላ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡ ከዛ በላይ መፍትሔ የለም፤ ቢኖር እነሱም ያቀርቡት ነበር፡፡” ያሉት ዋና ተደራዳሪው፤ “የሚፈለገውን መፍትሔ አስቀምጠናል፡፡ ነገር ግን እኛ ሀገር ላይ ጉዳት በሚያስከትል፣ ወይም ቀደም ሲል አለን በሚሉት የውሃ ኮታ መሰረት፣ ውሃውን ሙሉ በሙሉ ከተካፈሉ በኋላ ኢትዮጵያ ይሄን አረጋግጣ እንድትሰጣቸው የመፈለግ አካሔድ የትም ሊደርስ አይችልም፡፡ ትክክለኛም አይደለም፤ እኛ ሀገር ሊያሰቅል ይችላል፡፡ የትም ሀገር ቢሆን ሃብቱን ሙሉ በሙሉ አሳልፎ አይሰጥም፡፡ እንደላይኛው ተፋሰስ እኛ ብቻችንን እንጠቀም አላልንም፡፡ ተካፍለን አብረን እንልማ የሚል አቋም ነው ያለን፡፡” ብለዋል።

“ኢትዮጵያ በድርድር ሽፋን፣ በኣባይ ወንዝ ላይ ከቁጥጥር ውጭ የኾነ ባለቤትነት እንዳላት፣ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ይኹንታ ለማግኘት ብቻ መደራደርን መርጣለች፤” ያለው የግብጽ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር፣ “ግብጽ በዓለም አቀፍ ቻርተሮች እና ስምምነቶች መሠረት፣ በውኃዋ እና ብሔራዊ ደኅንነቷ ላይ ጉዳት በሚደርስበት ጊዜ ጥቅሟን የመከላከል መብቷ የተጠበቀ ነው፤” ሲልም አስጠንቅቋል፡፡

“ኢትዮጵያ በድርድር ሽፋን፣ በኣባይ ወንዝ ላይ ከቁጥጥር ውጭ የኾነ ባለቤትነት እንዳላት፣ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ይኹንታ ለማግኘት ብቻ መደራደርን መርጣለች፤”

ኢትዮጵያ በበኩሏ፣ በግድቡ ላይ የሚደረገው ድርድር፣ በሦስቱ ሀገራት መካከል መተማመን ለመፍጠር ያለመ እንጂ፣ “በዓባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ የኢትዮጵያን መብቶች ለማስነጠቅ አይደለም፤” ብሏል። የግብጽ መግለጫ፣ “የተባበሩት መንግሥታትን ቻርተር እና የአፍሪካ ኅብረትን ድንጋጌ የሚፃረር” እንደኾነም ሚኒስቴሩ ተችቷል፡፡ ኢትዮጵያ፣ የውኃ ሀብቷን፥ “ፍትሐዊ እና ምክንያታዊ በኾነ መንገድ፣ የአኹንና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት መጠቀሟን ትቀጥላለች፤” ሲልም አክሏል፡፡

አምባሳደር ስለሺ በቀለ በዛሬው መግለጫቸው፣ በድርድሩ ላይ ግብጽ፣ “ነባሩን የቅኝ ግዛት ዘመን የውኃ ክፍፍል የሚያንጸባርቅ” ሐሳብ በተደጋጋሚ ከማንሣቷም በላይ፣ “ቀጣይ ድርድር የማድረግ ፍላጎት እንደሌላትም ይፋ አድርጋለች፤” ብለዋል፡፡ ይኹንና ቀጣይ የድርድሩ ሒደት፣ በአፍሪካ ኅብረት መሪነት ሊቀጥል እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ የግንባታ መጠን፣ ከ94 በመቶ በላይ መድረሱን የገለጹት ዋና ተደራዳሪው አምባሳደር ስለሺ በቀለ(ዶር.)፣ ተጨማሪ አምስት ተርባይኖችም፣ በዚኽ ዓመት ኀይል ማመንጨት ይጀምራሉ፤ ሲሉ አክለው ገልጸዋል፡፡

የሕዳሴው ግድብ ላይ ድርድር ዛሬ ተጀምሯል

ፎቶ ፋይል - የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል - የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ

ግብጽ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን፣ ኢትዮጵያ እየገነባች ባለችው የህዳሴ ግድብ ላይ የሚያደርጉትን አራተኛ ዙር ድርድር ዛሬ አዲስ አበባ ላይ መጀመራቸውን ኢትዮጵያን የሚወክሉት ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ስለሺ በቀለ በ X ማኅበራዊ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል።

ሶስቱ ወገኖች ባለፈው መስከረም አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ሶስተኛ ዙር ድርድር ካለ ውጤት ተበትኖ እንደነበር ይታወሳል።

ድርድሮቹ በመደረግ ላይ ያሉት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እና የግብጹ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደል ፋታህ አል ሲሲ፣ በኢትዮጵያ እየተገነባ ባለው የህዳሴ ግድብ ጉዳይ፣ በአራት ወራት ውስጥ ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ ባለፈው ሐምሌ ማስታወቃቸውን መሠረት አድርጎ ነው።

አራተኛው እና በአዲስ አበባ በመቀጠል ላይ ያለው ድርድር፣ ከዚህ ቀደም በተደረጉ ድርድሮች እና ትናንት እሁድ በቴክኒካዊ ቡድኑ በተደረጉ ውይይቶች ላይ እንደሚመሠረት አምባሳደር ስለሺ ጨምረው አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ የምትመራው ግድቡን በተመለከተ እ.አ.አ 2015 በተደነገገው የመርህ ስምምነት እንዲሁም በጋራ እና በእኩልነት ላይ በተመሠረተ አጠቃቀም መሆኑንም አምባሳደሩ ገልጸዋል።

4.6 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው ግድብ ፍላጎቷን ከግምት ውስጥ የማያስገባ ከሆነ፣ የናይልን ወንዝ ለግብርና እና 100 ሚሊዮን ለሚሆን ሕዝቧ የውሃ ፍጆታ የምትጠቀመው ግብጽ ትልቅ ስጋት እንደሚሆንባት ስትገልጽ ቆይታለች

አብዛኛው የሀገሪቱ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ባለመሆኑ፣ ግድቡ አስፈላጊ እንደሆነ ኢትዮጵያ በበኩሏ ትገልጻለች፡፡

አራተኛውን ዙር የግድቡ ሙሌት ባለፈው 2015 መጨረሻ ላይ እንዳጠናቀቀች ኢትዮጵያ ማስታወቋ አይዘነጋም።

የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል

የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:59 0:00

በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጉዳይ፣ በዐዲስ አበባ የተደረገው ውይይት ያለስምምነት ለመጠናቀቁ፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ አንዳቸው ሌላቸውን ወቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ በድርድሩ የሚሳተፈው “የግብጽ ወገን፣ የ2015ቱን የመርሖዎች ስምምነት የማፍረስ አቋሙን ገፍቶበታል፤” ብሏል።

የግብጽ የመስኖ እና የውኃ ሚኒስቴር ደግሞ፣ ኢትዮጵያ፣ “ምንም ዐይነት ስምምነትን ትቃወማለች፤” ሲል ወቅሷል።

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚህ ሹክሪ፣ ለቪኦኤ በሰጡት አስተያየት፣ ለድርድሩ መጓተት ኢትዮጵያ የምትከተለውን መንገድ ተጠያቂ አድርገዋል።

በሌላ በኩል፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን አባል ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ድርድሩ ውጤታማ ያልኾነው በግብጽ ምክንያት እንደኾነ ገልጸዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ግብጽ የሕዳሴው ግድቡን አራተኛ ሙሌት “ሕገ ወጥ” ስትል አወገዘች

ፎቶ ፋይል፦ የኢትዮጵያ፣ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል፦ የኢትዮጵያ፣ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ

ኢትዮጵያ፣ የታላቁ የሕዳሴ ግድብን አራተኛ ሙሌት እንዳጠናቀቀች ስታስታውቅ፣ ግብጽ በበኩሏ፣ “ሕገ ወጥ ነው” ስትል አወገዘች፡፡

ሚኒስቴሩ፣ ትላንት እሑድ፣ ጳጉሜን 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ዐዲስ አበባ፣ የግድቡን ሙሌት ለማጠናቀቅ የወሰደችው “የተናጠል” ውሳኔ፣ “እ.ኤ.አ በ2021 ዓ.ም ተቋርጦ ባለፈው ወር ዳግም የተጀመረውን የሦስትዮሽ ድርድር ወደ ጎን የተወ ነው፤” ማለቱን አሶሺዬትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ “በውስጥ ፈተና፣ በውጭ ጫና ነበረብን። ከፈጣሪ ጋራ የመጣውን ሁሉ ተቋቁመን ለዚኽ ደርሰናል፤” ሲሉ፣ የሕዳሴ ግድቡ አራተኛ ሙሌት እንደተጠናቀቀ፣ ትላንት እሑድ፣ በፌስቡክ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በካርቱም በሦስቱ ሀገራት የተፈረመው የ2015 የመርሖዎች ስምምነት፣ ሦስቱ ሀገራት፥ በሕዳሴ ግድቡ ሙሌት እና የመተዳደሪያ ደንቦች ላይ መስማማት እንዳለባቸው የደነገገውን አስታውሷል፡፡

አያይዞም፣ “የኢትዮጵያ የአንድ ወገን አካሔድ፣ በዓለም አቀፍ ሕግ የተደነገጉ የተፋሰሱን የታችኛው ሀገራት መብት እና ጥቅም፣ እንዲሁም የውኃ ደኅንነታቸውን ወደ ጎን የተወ ነው፤” ሲልም ተችቷል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከግብጽ በኩል ስለቀረበው ወቀሳ እስከ አሁን በይፋ የሰጠው ምላሽ የለም፡፡

ኾኖም፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ(ዶር.)፣ ባለፉት አራት ዓመታት፣ የውኃ ሙሌት ሥራውን ለማከናወን የሚያስችል በቂ የዝናም መጠን እንደተገኘና በታችኛው ተፋሰስ ሀገራትም ላይ ምንም ዐይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ እንደተከናወነ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የግድቡ የውኃ ሙሌት፣ ከግንባታው ሒደት ጋራ ጎን ለጎን እንደሚከናወን የምትገልጸው ኢትዮጵያ፣ ይህም፣ ሦስቱ ሀገራት በተፈራረሙት የመርሖዎች ስምምነት መሠረት እንደሚፈጸም በተደጋጋሚ አስታውቃለች፡፡

በአፍሪካ ኅብረት አመቻችነት የሚካሔደው የሦስትዮሽ ድርድር፣ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 2021 ከተቋረጠ በኋላ፣ በነሐሴ ወር በካይሮ አስተናጋጅነት የተካሔደው ውይይትም፣ ተጨባጭ ውጤት እንዳላመጣ ግብጽ ይፋ አድርጋለች፡፡ ለዚኽም “ግትር አቋም ይዛለች፤” ያለቻትን ኢትዮጵያን ተጠያቂ አድርጋለች፡፡

ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለ ግብጽ ወቀሳ እና ትችት ጥያቄ የተነሣላቸው፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም፣ ውድቅ አድርገውታል፡፡

ኢትዮጵያ፣ በግድቡ ጉዳይ ሦስቱንም ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ እንደኾነች የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ በካይሮው ውይይት ላይ፣ “ግብጽስ ከቀድሞው የተለየ ምን አቋም አራምዳለች?” በሚል መጠየቅ እንዳለባት አመልክተዋል፡፡

በአወዛጋቢው የሕዳሴ ግድብ ውኃ ሙሌት ጉዳይ፣ ቀጣይ ዙር የሦስትዮሽ ውይይት፣ በዐዲስ አበባ እንደሚካሔድ ይጠበቃል፡፡

ሀመር በኅዳሴ ጉዳይ አውሮፓ ናቸው

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር በዚህ ሳምንት ወደ ስቶክሆልም እና ብራስልስ ተጉዘው በኅዳሴ ግድብ እና እንዲሁም ኢትዮጵያ እና ሱዳን ውስጥ እየተካሄዱ ባሉት ግጭቶች ዙሪያ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የስቶክሆልሙ ዓለም አቀፍ የውሃ ጉዳይ ተቋም በሚያስተናግደው የዓለም የውሃ ሳምንት ጉባዔ ላይ የሚካፈሉት አምባሳደር ማይክ የስቶክሆልም ዓለም አቀፍ የሰላም እና ምርምር ተቋም በሚያስተናግደው ውይይት ላይም እንደሚካፈሉ ተመልክቷል፡፡

ሀመር የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዋናው የዩናይትድ ስቴትስ መልዕክተኛ እንደመሆናቸው የውሃ አያያዝ፣ አጠቃቀም እና ተደራሽነትነት የሚመለከቱ ሥምምነቶች ለአፍሪካ ቀንድ ጸጥታ እና መረጋጋት ሊያበረክቱ ስለሚችሉት አስተዋጻኦ እንደሚወያዩ ተገልጿል፡፡ በመቀጠል ወደብረሰልስ በማቅናት ኢትዮጵያን እና ሱዳንን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከአውሮፓ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር እንደሚወያዩ ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡

አምባሳደር ሀመር በኢትዮጵያ ጉዳይ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች በውይይት ለመፍታት ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ሕብረት እንዴት ሊደግፉ እንደሚችሉ፤ በተጨማሪም ለሰላማዊ ዜጎች በሚደረግ ጥበቃ አስፈላጊነት ዙሪያም እንደሚወያዩ ተገልጧል።

ልዩ መልዕክተኛው ከአውሮፓ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር ሚያደርጓቸው ውይይቶች የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ለማስቆም ምክኒያት የሆነው ሥምምነት በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እና በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን በሙሉ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሰላም፣ ፍትህ እና ተጠያቂነትን ለማስፈን በሚሰጡት ድጋፍ ዙሪያም ይመክራሉ ተብሏል።

አምባሳደር ሀመር በሱዳኑ ግጭት የአፈሙዞች ላንቃ እንዲዘጋ፤ ተጠያቂነትን ለማስከበር እና ዲሞክራሲያዊ የሲቪል አስተዳደር ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ የተያዙ አህጉራዊ እና አለምአቀፋዊ ጥረቶች ዙሪያም ይወያያሉ። ለክልሉ የሚሰጠውን ሰብአዊ ድጋፍ ለማጠናከር የተያዘው ሥራ ማቀላጠፉ እንደሚቀጥልም መግለጫው ጠቅሷል።

የሕዳሴ ግድብ ውይይት በአራት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ መሪዎቹ አስታወቁ

የሕዳሴ ግድብ ውይይት በአራት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ መሪዎቹ አስታወቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:24 0:00

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስምምነትን፣ በአራት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሠሩ፣ የኢትዮጵያ እና የግብፅ መሪዎች እንዳስታወቁ ሮይተርስ ዘግቧል።

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተደራዳሪ ቡድን አባል ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ፣ ይህ የሮይተርስ ዜና ከመሰማቱ አስቀድሞ በሰጡን አስተያየት፣ “ድርድሩ ረዘም ያለ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል” አመልክተዋል፡፡

የውኃ ሙሌቱ፣ ከግድቡ የግንባታ ሒደት ጋራ በተጣጣመ መልኩ እንደሚከናወን የገለጹት ፕር. ይልማ፣ የክረምቱ መራዘም፣ ግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመሩ እና ከፍታው መጨመሩ፣ በሚያዘውና በሚለቀቀው የውኃ መጠን ላይ ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የግብጹ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታሕ አል-ሲሲ፣ ካይሮ ላይ ተገናኝተው፣ በኢትዮጵያ በመገንባት ላይ ስላለው የሕዳሴ ግድብ የውኃ አሞላል እና በሥራ ላይ በሚውልበት ጊዜ የሚኖረውን የአጠቃቀም ደንብ በተመለከተ፣ ሱዳንን ጨምሮ በሦስቱ አገሮች መካከል ሲደረግ የነበረውንና የተቋረጠውን ድርድር በአራት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ተስማምተዋል።

የሮይተርስ ዜና ወኪል፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል የወጣውን የጋራ መግለጫ ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ሁለቱ መሪዎች፣ ስምምነቱን በአራት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተስማማተዋል፤ ተብሏል።

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የግብጹ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታሕ አል-ሲሲ፣ ትላንት ረቡዕ፣ ካይሮ ላይ ተገናኝተው፣ በኢትዮጵያ በመገንባት ላይ ስላለው የሕዳሴ ግድብ፣ እንዲሁም በሱዳን በተፈጠረው ቀውስ ላይ እንደተነጋገሩ፣ የግብጹ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት አስታውቋል።

አል-ሲሲ፣ ዐቢይ አሕመድን በቤተ መንግሥታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውን ጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል።ሁለቱ መሪዎች ካይሮ ላይ የተገናኙት፣ በአል-ሲሲ አስተናጋጅነት፣ ስድስት የሱዳን ጎረቤት ሀገራት፣ ለ12 ሳምንታት የዘለቀውን የሱዳን ግጭት አስመልክቶ ለመነጋገር፣ ካይሮ ላይ ካደረጉት ስብሰባ ጎን ለጎን ነው።

ሙሉ ዘገባን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:33 0:00

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ

ፎቶ ፋይል፦ የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል፦ የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ

የውሃ ሙሌቱ መጠናቀቅ “የዲፕሎማሲውን በር በሰፊው የሚከፍት ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጉባ ተራራዎች ስር፣ መጋቢት 24/2003 ዓ.ም የመሰረት ድንጋዩ ከተቀመጠለት ጊዜ ጀምሮ ሦስት መሪዎች የተፈራረቁበት እና አሁንም በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቁ ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡

የግድቡ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቆ ውሃው ከዛሬ ነሐሴ 6 ጀምሮ በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ መጀመሩን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሥፍራው አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ የጋራ ሀብታቸው የሆነውን የዓባይን ወንዝ በትብብር ሊጠቀሙ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የግድቡ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት የተከናወነው፣ በኢትዮጵያ፣ በግብጽ እና ሱዳን መካከል ያለው አለመግባባት ተባብሶ በቀጠለበት ወቅት ነው፡፡

የግድቡ እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ በአባይ ተፋሰስ የግርጌ ሃገሮች መካከል ትብብር እንዲኖር “የዲፕሎማሲውን በር በሰፊው የሚከፍት ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ተናግረዋል፡፡ ግድቡ ኃይል ከማመንጨት ያለፈ ሀገራዊ ትርጉም እንዳለውም ያነሱት ፕሬዚዳንቷ፣ ይሄውም “ኢትዮጵያውያን ከተባበርን ለዚህ መድረስ እንችላለን የሚል ነው" ብለዋል፡፡

3ኛውን ዙር የግድቡን የውሃ ሙሌት በመቃወም ግብጽ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ለመንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ደብዳቤ ያስገባች ሲሆን “በግብፅ ጥቅም ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም ጉልህ ጉዳት ኢትዮጵያ ሙሉ ኃላፊነት ትወስዳለች” ስትል በደብዳቤዋ ገልጻለች።

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:33 0:00

ሥምምነት የራቀው እና በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ሲካሔድ የነበረው የሦስትዮሽ ድርድርም ከተቋረጠ ቆይቷል፡፡ ሀገራቱ ለመጨረሻ ጊዜ ለድርድር የተቀመጡት በሚያዝያ ወር 2013 ዓ.ም ነው፡፡

ኢትዮጵያ በግድቡ የውሃ ሙሌት እና ከግድቡ በሚለቀቀው የውኃ መጠን ላይ አስገዳጅ ስምምነት እንድትፈርም የሚፈልጉት ግብጽና ሱዳን እስካሁን ለተካሔዱት ድርድሮች አለመሳካት ግትር አቋም ይዛለች በማለት ኢትዮጵያን ተጠያቂ ያደርጋሉ፡፡ በተቃራኒው ግትር አቋም የያዙት ግብጽና ሱዳን መሆናቸውን የምትገልጸው ኢትዮጵያ ለድርድሩ ውጤታማ አለመሆን ጣቷን የምትቀስረው በሁለቱ ሀገራት ላይ ነው፡፡

የግድቡን ሦስተኛ ዙር ሙሌት በማስመልከት ንግግር ያደረጉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ ወቅታዊው የግድቡ ሁኔታ የሁለቱ ሀገራት ክስ ሐሰት መሆኑን እንደሚያጸባርቅ አመለክተዋል፡፡

በግድቡ ጉዳይ በሦስቱ ሀገራት መሃከል ያለው ልዩነት በንግግር እንዲፈታ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በመጠየቅ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በቅርቡ በካይሮ እና በአዲስ አበባ ጉብኝት ያደረጉት የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመርም ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ እና የኢትዮጵያ የልማት ፍላጎት በሰፊው መረዳታቸውን ገልጸው፣ በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ሥር በሚካሔደው የዲፕሎማሲ ጥረት፣ ሁሉንም የተፋሰሱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ ሥምምነት ላይ መድረስ ይቻላል ብለዋል።

በ2012 የክረምት ወቅት ላይ 4.9 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በመያዝ ሙሊቱ የተጀመረው የኅዳሴው ግድብ፣ አሁን በሦስተኛው ዙር የያዘው የውኃ መጠን 22 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ግድቡ ሙሉ ለሙሉ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የሚይዘው የውሃ መጠን 74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ አጠቃላይ የማመንጨት አቅሙ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት ነው።

ከኅዳሴ ግድቡ 13 የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች መካከል፣ 9ኛው ዩኒት ትናንት ሥራ የጀመረ ሲሆን 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ በሙሉ አቅሙ የማመንጨት ደረጃ ላይ እስኪደርስ አሁን ላይ እስከ 270 ሜጋ ዋት እንደሚያመነጭ ተገልጿል፡፡ ተመሳሳይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው 10ኛው ዩኒት ባለፈው የካቲት 13/2014 ዓ.ም ሥራ መጀመሩ ይታወሳል፡፡

የግድቡ አጠቃላይ የግምባታ አፈጻጸም 83 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን ያስታወቁት ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፣ በ 2 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የግድቡ ግምባታ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡

ከአፍሪካ ትልቁ የውኃ ኃይል ማመንጫ የሆው የኅዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ 145 ሜትር ከፍታ እና 1,780 ሜትር ርዝማኔ ይኖረዋል፡፡ ውሃው ከግድቡ ወደ ኋላ 240 ኪሎ ሜትር ድረስ እንደሚያርፍም ይጠበቃል፡፡

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:00 0:00

ሁለተኛው እና 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኅዳሴ ግድብ ተርባይን የኤሌክትሪከ ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ዛሬ ይፋ ተደረገ። አጠቃላይ ግንባታው በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።

ሦስተኛው ሙሌት በሂደት ላይ መሆኑን የገለጹት የኅዳሴ ግድቡ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የግድቡን ሁለተኛ ዩኒት የኤሌክትሪከ ኃይል ማመንጫ ሥራ ያስጀመረችው ከአባይ ተፋሰስ የግርጌ ሃገሮች ማለትም ግብጽ እና ሱዳን ጋር ያላት አለመግባባት ተባብሶ በቀጠለበት ወቅት ነው፡፡

ኢትዮጵያ ከእነዚህ ሃገሮች ጋራ ስምምነት ላይ ሳትደርስ ኅዳሴ ግድብን ለሦስተኛ ጊዜ መሙላት ልትጀምር ነው ስትል ግብፅ በቅርቡ ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ተቃውሞ ማቅረቧን ይታወሳል።

በአፍሪካ አቻ የሌለው ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ይሆናል የተባለው ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ በተለይ በኢትዮጵያና በሁለቱ የግርጌ ሃገሮች መካከል የውጥረትና የንትርክ ሰበብ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።

ዛሬ ሁለተኛውን የኅዳሴ ግድብ ተርባይ የኤሌክትሪከ ኃይል ማመንጫ መርቀው የከፈቱት

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀገራቸው የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት የመጉዳት ፍላጎት እንደሌላት ገልጸው፣ ከውይይት ውጭ የሚወሰድ እርምጃ ማንንም እንደማያዋጣ ተናግረዋል።

የዛሬ አሥራ አንድ ዓመት የተጀመረው ከአራት ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው የኅዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ 5000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል።

/ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:00 0:00

ግብፅ የኅዳሴ ግድብን ሦስተኛ ሙሌት ተቃወመች

ፎቶ ፋይል፦ ኅዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል፦ ኅዳሴ ግድብ

ኢትዮጵያ ከዓባይ ተፋሰስ የግርጌ ሃገሮች ጋር ስምምነት ላይ ስትደርስ ኅዳሴ ግድብን ለሦስተኛ ጊዜ መሙላት ልትጀምር ነው ስትል ግብፅ ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ተቃውሞ ማቅረቧን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ።

በአፍሪካ አቻ የሌለው ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ይሆናል የተባለው ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ በተለይ በኢትዮጵያና በሁለቱ የግርጌ ሃገሮች መካከል የውጥረትና የንትርክ ሰበብ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።

ኢትዮጵያ በዚህ ክረምት ግድቡን መሙላት እንደምትቀጥል የሚያሳውቅ ድብዳቤ ባለፈው ሣምንት ማክሰኞ ለግብፅ መላኳንና ካይሮም መልዕክቱ እንደደረሳት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መናገሩን ግብፅም የተቃውሞ አቤቱታዋን ይዛ ወደ መንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታ ምክር ቤት መሄዷን ኤኤፍፒ አክሎ ጠቁሟል።

የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማከልም “ግብፅ ብሄራዊ ደኅንነቷን ለማስከበርና ወደፊት ኢትዮጵያ በተናጠል በምትወስዳቸው እርምጃዎች ምክንያት የሚመጡ አደጋዎችን ለመከላከል ህጋዊ መብቷን ተጠቅማ አስፈላጊውን እርምጃ ትወስዳለች” ብሏል።

የዛሬ አሥራ አንድ ዓመት የተጀመረው ከአራት ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው የኅዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ 5000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል።

ዛሬ፤ ሰኞ ከግብፅ ባለሥልጣናት ጋር የተነጋገሩትና ባለፈው ዓርብ ኢትዮጵያ የነበሩት የዩናይትድ ስቴትስ አዲሱ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሃመር የአሁን ጉብኝት ዝርዝር ለጊዜው ባይገለፅም ውይይቶቻቸው አጨቃጫቂውን የኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ሳይጨምር እንደማይቀር ተነግሯል።

የኅዳሴ ተርባይን መንቀሳቀስ፣ የግብፅና የሱዳን ቅሬታና የባለሙያ ትንታኔ

የኅዳሴ ተርባይን መንቀሳቀስ፣ የግብፅና የሱዳን ቅሬታና የባለሙያ ትንታኔ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:54 0:00

ሱዳን የታችኛው ተፋሰስ አገሮች ሳይስማሙ “በተናጠል የተፈፀመ ባለችው” እርምጃ ኢትዮጵያ ከኅዳሴ ግድም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መጀመሯን በመቃወውም ውግዘት አሰማች።

የሱዳኑ ተደራዳሪ ቡድን ቃል አቀባይ ኦማር ካሚል “ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብን ለመሙላት የተወሰዱትን ሁሉንም እርምጃዎች ሱዳን በአፅንዖት ታወግዛለች” ብለዋል።

“ኢትዮጵያ የወሰደችው እርምጃ በዓለም አቀፍ ህግጋት ያሉባትን ግዴታዎች የሚጥስ ነው” ብለዋል።

የግድቡን ግንባታ አምርራ ስትቃወም የቆየችው ግብፅም ኢትዮጵያ የግድቡን አንድ የኃይል ማመንጫ ተርባይን ማንቀሳቀሷን በመተቸት መግለጫ አውጥታለች።

ሦስቱ አገሮች በግድቡ ዙሪያ ላለፉት አሥራ አንድ ዓመታት ሲደራደሩ ቢቆዩም አንዳች ስምምነት ላይ መድረስ አልቻሉም።

ግብፅና ሱዳን ግድቡ በሚሞላበት ሁኔታ ላይም ይበጀናል ባሉት መንገድ ስምምነት ላይ እንዲደረስ ግፊት ማድረጋቸውን የጠቀሰው የአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገባ የተፈለገው ስምምነት ላይ ባይደረስም ኢትዮጵያ በ2012 ዓ.ም. ክረምት ግድቡን መሙላት መጀመሯን አስታውሷል።

ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በአፍሪካ አቻ የለሽ የሚሆነው ኅዳሴ በሕዝቧ ቁጥር በአህጉሩ ሁለተኛ ትልቅ አገር የሆነችው ኢትዮጵያ ለልማቷ ቁልፍ እንደሆነ ትናገራለች።

በሌላ በኩል ዘጠና ከመቶ የመስኖና የንፁህ ውኃ አቅርቦቷ ምንጭ አባይ የሆነው ግብፅ የኅዳሴ ግድብን ግንባታ የሕልውናዋ አደጋ አድርጋ ታያለች ያለው የኤኤፍፒ ዘገባ ሱዳን በአንፃሩ በያመቱ የሚገጥማትን በጎርፍ የመጥለቅለቅ አደጋ ይቆጣጠራል የሚል ተስፋ ቢኖራትም በሦስቱ ሃገሮች መካከል ስምምነት ካልተደረሰ የራሷ ግድብ ይጎዳል የሚል ስጋት እንዳላት አመልክቷል።

ግብፅ ያሰማችውን ውንጀላ ተንተርሶ የአሜሪካ ድምጽ ለትንታኔ የጋበዛቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስና የዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህሩ የዓለም አቀፍ የውኃ ጉዳዮች አዋቂው ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ “በህዳሴ ግንባታም ሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በተከናወነው ሥራ የተጣሰ ምንም ዓይነት ስምምነት የለም” ይላሉ።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG