በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል


የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:59 0:00

የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል

በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጉዳይ፣ በዐዲስ አበባ የተደረገው ውይይት ያለስምምነት ለመጠናቀቁ፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ አንዳቸው ሌላቸውን ወቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ በድርድሩ የሚሳተፈው “የግብጽ ወገን፣ የ2015ቱን የመርሖዎች ስምምነት የማፍረስ አቋሙን ገፍቶበታል፤” ብሏል።

የግብጽ የመስኖ እና የውኃ ሚኒስቴር ደግሞ፣ ኢትዮጵያ፣ “ምንም ዐይነት ስምምነትን ትቃወማለች፤” ሲል ወቅሷል።

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚህ ሹክሪ፣ ለቪኦኤ በሰጡት አስተያየት፣ ለድርድሩ መጓተት ኢትዮጵያ የምትከተለውን መንገድ ተጠያቂ አድርገዋል።

በሌላ በኩል፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን አባል ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ድርድሩ ውጤታማ ያልኾነው በግብጽ ምክንያት እንደኾነ ገልጸዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG