በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሕዳሴው ግድብ ላይ ድርድር ዛሬ ተጀምሯል


ፎቶ ፋይል - የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል - የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ

ግብጽ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን፣ ኢትዮጵያ እየገነባች ባለችው የህዳሴ ግድብ ላይ የሚያደርጉትን አራተኛ ዙር ድርድር ዛሬ አዲስ አበባ ላይ መጀመራቸውን ኢትዮጵያን የሚወክሉት ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ስለሺ በቀለ በ X ማኅበራዊ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል።

ሶስቱ ወገኖች ባለፈው መስከረም አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ሶስተኛ ዙር ድርድር ካለ ውጤት ተበትኖ እንደነበር ይታወሳል።

ድርድሮቹ በመደረግ ላይ ያሉት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እና የግብጹ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደል ፋታህ አል ሲሲ፣ በኢትዮጵያ እየተገነባ ባለው የህዳሴ ግድብ ጉዳይ፣ በአራት ወራት ውስጥ ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ ባለፈው ሐምሌ ማስታወቃቸውን መሠረት አድርጎ ነው።

አራተኛው እና በአዲስ አበባ በመቀጠል ላይ ያለው ድርድር፣ ከዚህ ቀደም በተደረጉ ድርድሮች እና ትናንት እሁድ በቴክኒካዊ ቡድኑ በተደረጉ ውይይቶች ላይ እንደሚመሠረት አምባሳደር ስለሺ ጨምረው አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ የምትመራው ግድቡን በተመለከተ እ.አ.አ 2015 በተደነገገው የመርህ ስምምነት እንዲሁም በጋራ እና በእኩልነት ላይ በተመሠረተ አጠቃቀም መሆኑንም አምባሳደሩ ገልጸዋል።

4.6 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው ግድብ ፍላጎቷን ከግምት ውስጥ የማያስገባ ከሆነ፣ የናይልን ወንዝ ለግብርና እና 100 ሚሊዮን ለሚሆን ሕዝቧ የውሃ ፍጆታ የምትጠቀመው ግብጽ ትልቅ ስጋት እንደሚሆንባት ስትገልጽ ቆይታለች

አብዛኛው የሀገሪቱ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ባለመሆኑ፣ ግድቡ አስፈላጊ እንደሆነ ኢትዮጵያ በበኩሏ ትገልጻለች፡፡

አራተኛውን ዙር የግድቡ ሙሌት ባለፈው 2015 መጨረሻ ላይ እንዳጠናቀቀች ኢትዮጵያ ማስታወቋ አይዘነጋም።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG