በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ያለስምምነት በተጠናቀቀው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ግብጽ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌላት ተገለጸ


ያለስምምነት በተጠናቀቀው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ግብጽ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌላት ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:53 0:00

በዐዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ቀናት የተካሔደው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛው ዙር ድርድር፣ ያለስምምነት እንደተጠናቀቀ፣ ትላንት ያስታወቁት ኢትዮጵያ እና ግብጽ፣ ለውጤት አልባነቱ አንዳቸው ሌላቸውን ወንጅለዋል፡፡

ግብጽ፥ “ውይይቱ ያልተሳካው ኢትዮጵያ ምንም ዐይነት ስምምነት ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመኾኗ ነው፤” ስትል፤ ኢትዮጵያም በበኩሏ፣ “የስምምነቱን መንገድ የዘጋችው ግብጽ ናት፤” ብላለች፡፡

በድርቅ ወቅት የሚኖረው የውኃ አያያዝ እና አለቃቀቅ፣ በድርድሩ ከፍተኛ ልዩነት የታየበት ጉዳይ እንደነበረ፣ የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ዶር. ስለሺ በቀለ ገልጸዋል፡፡

ግብጽ፣ “ከዚኽ በኋላ ድርድሩን የመቀጠል ፍላጎት የለኝም፤” እንዳለች የገለጹት አምባሳደር ስለሺ፣ የአፍሪካ ኅብረት ዳግም ወደ አደራዳሪነቱ ሊመለስ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

XS
SM
MD
LG