በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፓልሚራን ከአይሲስ ያስለቀቀው የሶሪያ ጦር የቀጣይ ዘመቻዬ መነሻ ናት አለ


የፓልሚራ ከተማ ወፍ በረር እይታ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:01 0:00

استقبال پرزیدنت ترامپ و بانوی اول از فیلیپ ششم، پادشاه اسپانیا به همراه همسرش در کاخ سفید<br /> &nbsp;

“የሶሪያ መንግስት ኃይሎች በፓልሚራ አይሲስ’ን ድል ለመንሳትና ብሎም ቡድኑ ያወደመውን መልሶ ለመገንባት የያዙት እቅድ በሰብዓዊነት ላይና በባሕል እሴቶች ላይ የተቃጣን ለመከላከል መቻሉ አበረታች ነው። የተናገሩትን ተግባራዊ ማድረግ ይሳካላቸዋል ብዬም ተሥፋ አደርጋለሁ።” የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ባን ኪሙን

የፓልሚራን ከተማ ከእስላማዊው ጽንፈኛ አይሲስ እጅ አውጥቶ መልሶ የተቆጣጠረበትን ድል፤ በቡድኑ ላይ ለሚያካሂደው ቀጣይና መጠነ-ሠፊ ዘመቻ የማቀናበባበሪያ መነሻ ጭምር ሊያደርገው ማቀዱን የሶሪያ ጦር ሠራዊት አስታወቀ።

የአገሪቱ ጥንታዊ ቅርሶች ጥበቃ ተቋም ተጠሪ በበኩላቸው፤ “ከቡድኑ የከፋ የጥቃት የተረፈው ይህ ታሪካዊ ሥፍራ ሌላ ይበልጥ አስፈላጊና የላቀ ጠቀሜታም አለው፤” ይላሉ። የሶሪያ መንግስት ኃይሎች በሩሲያ የዓየር ድብደባ እየታገዙ፤ ከሁለት ሺህ ዓመታት እድሜ በላይ ባስቆጠሩ ሃውልቶች ላይ ያደረሰውን እጅግ የከፋ ውድመት ጨምሮ ጽንፈኛው ቡድን በጥንታዊቱ የፓልሚራ ከተማ አስፍኖት ለነበረውና ለአሥር ወራት ለዘለቀው ቁጥጥር ማብቂያ አበጅተዋል።

ዋና መቀመጫውን በብሪታንያ ያደረገው የሶሪያ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ቡድን ይፋ እንዳደረገው፤ ፓሊሚራ’ን ከቡድኑ እጅ ለማስለቀቅ በተካሄደው ውጊያ ቁጥራቸው ከአራት መቶ በላይ የሚደርስ የሸማቂው ቡድን ተዋጊዎችና ሌሎች ቁጥራቸው ከ180 በላይ የሚደርስ የመንግስቱ ኃይሎች ተዋጊዎች ተገድለዋል።

ፓልሚራን ከአይሲስ ያስለቀቀው የሶሪያ ጦር የቀጣይ ዘመቻዬ መነሻ ናት አለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:44 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG