በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ውይይት ከሻለቃ ዳዊት ወልደ-ጊዮርጊስ ጋር


ሻለቃ ዳዊት ወልደ-ጊዮርጊስ ከቪኦኤው ስትሬት ቶክ አፍሪካ ጋር ቃለ-ምልልስ እያደረጉ እ.አ.አ. 2013
ሻለቃ ዳዊት ወልደ-ጊዮርጊስ ከቪኦኤው ስትሬት ቶክ አፍሪካ ጋር ቃለ-ምልልስ እያደረጉ እ.አ.አ. 2013

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ መከሰቱ፣ በዚህም ሚክንያት አያሌ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ለራብ መጋለጣቸው፣ ሕይወታቸውን ያጡም እንዳሉ፣ ድርቁም አስጊና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ የዓደባባይ ምስጢር ነው።

የዛሬ እንግዳችን ሻለቃ ዳዊት ወልደ-ጊዮርጊስ ናቸው። የውትድርናውን መጠሪያ ያገኙት ሐረር ጦር አካዳሚ ገብተው እስከ መቶ እልቅና እንደዘለቁ፣ ከዚያም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ህግ ከተማሩ በኋላ ሻለቃ እንደተባሉ አጫውተውናል። ይህ ነው የመለያ ማእረጋቸው ታሪክ።

የዛሬው ወጋችን ግን በሕይወት ታሪካቸው ማለትም ስለ አስተዳደጋቸው ወይም ስለ ትምህርት ቤት ሕይወታቸው ሳይሆን፣ (ያ ለሌላ ጊዜ ይቆየንና) ዛሬ የምናተኩረው ይበልጥ በሚታወቁበት በእርዳታ ማሰባበሪያና ማቋቋሚያ ኰሚሽን አገልግሎታቸው ዙሪያ ይሆናል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ መከሰቱ፣ በዚህም ሚክንያት አያሌ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ለራብ መጋለጣቸው፣ ሕይወታቸውን ያጡም እንዳሉ፣ ድርቁም አስጊና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ የዓደባባይ ምስጢር ነው።

በመሆኑም በዚህ አሳሳቢ ጉዳይ፣ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ እንግዶችን፣ ባለሙያዎችን እየጋበዝን አወያይተናል። ሻለቃ ዳዊትም ለዚህ ዓይነቱ ርዕስ ተገቢ እንደሚሆኑ በማመን፣ ከእርሳቸው ጋር ካደረግንው ሰፊ ውይይት፣ ለዛሬ በወቅታዊው ድርቅና ረሀብ፣ እንዲሁም በመፍትሔ ሃሳቡ ላይ ብቻ እናተኩራለን። ያወያያቸው አዲሱ አበበ ነው።

"በአሁኑ ወቅት የት ነው እንዴ ያሉት? ምንስ እየሠሩ ነው?" ብሎ ላቀረበላቸው ጥያቄ ከሰጡት መልስ እንነሳለን። ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

ውይይት ከሻለቃ ዳዊት ወልደ-ጊዮርጊስ ጋር
please wait

No media source currently available

0:00 0:20:57 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG