በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የምዕራብ አፍሪቃ አገሮች የኢቦላ ወረርሽኝ ዳግም ቢከሰት የመከላከል አቅማቸው እንደተሻለ የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪቃ ዲሬክተር አስታወቁ


ፋይል - የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪቃ ዲሬክተር ማትሺዲሶ ሞዊቲ
ፋይል - የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪቃ ዲሬክተር ማትሺዲሶ ሞዊቲ

​​ዲሬክተሩ ማትሺዲሶ ሞዊቲ በተለይ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የ2014ቱ ኢቦላ ወረርሽኝ ዋነኛ ተጠቂዎች፥ ላይቤሪያ፥ ሴራሊዮንና ጊኒ በበሽታዎች ክትትል፥ የላቦራቶር ምርመራ እና የጤና ክብካቤ አገልግሎት አቅማቸውን በወጉ በማጎልበታቸው ለመሰል ድንገተኛ ሁኔታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠት በሚያስችል ደረጃ ላይ ናቸው።

በኢቦላ ክፉኛ ተጠቅተው የነበሩት የምዕራብ አፍሪቃ አገሮች ወረርሽኙ ዳግም ቢከሰት ለመከላከል በሚያስችል አቅም ራሳቸውን የተሻለ አዘጋጅተዋል፤ ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪቃ ዲሬክተር አስታወቁ።

ፋይል ፎቶ - እ.አ.አ. በኢቦላ ቫይረስ የተጠቃ ህመምተኛ በፍሪታውን ሴራልዮን ውስጥ የሚገኝ ፖርት ሎኮ ማኅበረሰብ ተብሎ የሚጠራ ቤት ደጃፍ ተኝቶ
ፋይል ፎቶ - እ.አ.አ. በኢቦላ ቫይረስ የተጠቃ ህመምተኛ በፍሪታውን ሴራልዮን ውስጥ የሚገኝ ፖርት ሎኮ ማኅበረሰብ ተብሎ የሚጠራ ቤት ደጃፍ ተኝቶ

ዲሬክተሩ ማትሺዲሶ ሞዊቲ በተለይ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የ2014ቱ ኢቦላ ወረርሽኝ ዋነኛ ተጠቂዎች፥ ላይቤሪያ፥ ሴራሊዮንና ጊኒ በበሽታዎች ክትትል፥ የላቦራቶር ምርመራ እና የጤና ክብካቤ አገልግሎት አቅማቸውን በወጉ በማጎልበታቸው ለመሰል ድንገተኛ ሁኔታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠት በሚያስችል ደረጃ ላይ ናቸው።

ሊሳ ሽላይ ከጄኔቫ ለአሜሪካ ድምጽ ያጠናቀረችውን ዘገባ አሉላ ከበደ አቅርቦታል።

XS
SM
MD
LG