በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዑጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ኪዛ በሲጄ እንደገና ታሰሩ


የዑጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ኪዛ በሲጄ
የዑጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ኪዛ በሲጄ

የዑጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ኪዛ በሲጄ በዚህ ሳምንት ከእስር ተፈተዉ ነጻ መሆን ነበርባቸዉ ። ኪዛ በሲጄ ካለፈዉ የካቲት ወር አጋማሽ የዑጋንዳ ምርጫ ወዲህ በቤታቸዉ በቁም እስር ይገኛሉ። ሆኖም ትናንት ገና ከቤታቸዉ ወጣ ሲሉ እንደገና የፓሊስ ቁጥጥር ስር ዉለዋል።

የዑጋንዳ ባለስልጣናት የተቃዋሚ መሪዉ ኪዛ በሲጄ ትናንት ማክሰኞ በፓሪቲአቸዉ ማእከል በሚደረግ የጸሎት ስነስርዓት ላይ ሊገኙ እንደሚችሉነገርዋቸዉ ነበር። በሲጄወደ አንድ ቦታ ሲያመሩ ሕዝብ እርሳቸዉ መከተልየተለመደ ነዉ። ትናንትም ታዲያ ይሐዉ ነዉ የሆነዉ።

መሪዉ ከካምፓላ ወጣብሎ ከሚገኝ ቤታቸዉ ወደ መሃል ከተማ ሲያቀኑ ደጋፊዎቻቸዉ ተከተሏቸዉ። አንደኛ ደጋፊ በሲጄ እንደገና የታሰሩብን ሁኔታ ሲያስረዳ ገና መንገድ ስንጀምር ፓሊሶች የመረጥነዉን መንገድ ዘግተዉ እንዳናልፍ ከለከሉን። ወደ መሃል ከተማ የሚያመሩ መንገዶን ሁሉ ፓሊሶች አጠሩት ብሏል።

ፋይል ፎቶ - የኪዛ በሲጄ ደጋፊ
ፋይል ፎቶ - የኪዛ በሲጄ ደጋፊ

ፓሊሶቹ ወዲያዉ በሲጄን ቁጥጥር ስር አዉለዉ ከካምፓላ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ ናጋላማ ፓሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል። አንድ የፓሊስ ቃል አቀባይ በሲጄ በህገ ወጥ ሰልፍ በመሳተፍ ነዉ የተከሰሱት ብሏል።

የበሲጄ እስራት በደጋፊዎቻቸዉ ዘንድ ቁጣና ቀቢጸ ተስፋና ቁጣን አስከትሏል አንዱ እንዲህ ገልጸዉታል። "በገዛ አገራችን ባእድ እንደሆን ነዉ የሚሰማን፣ አገሪቱ የእኛም እንዳልሆነች።በእዉነቱ ፕሬዚደንት ዩዌሪ ካጉታ ሙሴቬኒ ይህቺን አገር የግላቸዉ ብቻ እንዳደረጓት ነዉ የሚሰማን፣ ዑጋንዳ የዑጋንዳዉያን ሁሉ መሆኗ ቀርቶ የእርሳቸዉና የቤተሰባቸዉ ብቻ።" ብለዋል።

በሲጄ ከየካቲቱ የአገሪቱ ምርጫ በፊትም አያሌ ጊዜያት ተስረዉ እንደነበር ድምጽ ከተሰጠበት ቀን በኋላም ለአንድ ወር ተኩል እንደታሰሩ ይታወቃል።ያን ምርጫ ስልሳ በመቶዉን ድምጽ አገኘሁ በማለት ፕሬዚደንት ሙሴቪኒ ማሸነፋቸዉና ለአምስተኛ ጊዜ ስልጣን መቆጣጠራቸዉ ይታወሳል። በሲጄ 35 በመቶዉን ድምጽ በማግነት ሁለተኛ ተብሎ ነበር፥ ምርጫዉ የተጭበረበረ መሆኑን ቢናገሩም እንዲታሰሩ ሰለተደረገ በፍርድ ቤት ሊከራከሩ አልቻሉም። የድምጽ ፋይሉን በመጫን የትናንትናውን ሙሉ ዘገባ ያድምጡ።

የዑጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ኪዛ በሲጄ እንደገና ታሰሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:46 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG