በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ እና የኬንያ አትሌቶች በተለያዩ ማራቶኖች ቀንቷቸዋል


የኬንያዋ ጀሚማ ሱምጎንግ እና የኢትዮጵያ ትግስት ቱፋ አትሌቶች በለንደን ማራቶን
የኬንያዋ ጀሚማ ሱምጎንግ እና የኢትዮጵያ ትግስት ቱፋ አትሌቶች በለንደን ማራቶን

የኢትዮጵያ ሴት አትሌቶች በማድሪዱ ማራቶን አሸነፉ። አስካለ ዓለማየሁ አንደኛ፥ አበበች ፀጋዬ ሁለተኛ ሆነዋል። የወንዶቹ በኬንያውያኑ የበላይነት ተጠናቀቀ። ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ሥፍራ ጠራርገው ወስደዋል።

የኬንያ አትሌቶች በለንደን ማራቶንም ቀንቷቸዋል። በሁለቱም ፆታዎች ነው ያሸነፉት። በተለይ የሴቶቹን ጀሚማ ሱምጎንግ (Jemima Sumgong) ውኃ ማደያው ሥፍራ ላይ ከኢትዮጵያዊቷ አሰለፈች መርጊያ ጋር ተጋጭታ ከወደቀች በኋላ ተነስታ ማሸነፏ፥ ብዙዎችን አስደንቋል።

በወንዶቹ ኢሉድ ኪፕቾጌ (Eluid Kipchoge) ሻምፒየንነቱን ተከላክሏል። በሌላ ያትሌቲክስ ስፖርት ዜና፥ በአዲስ አበባ ስታዲየም ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የሰነበተውን 45ኛ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር መከላከያ አሸንፏል።

ከሻባይት የመንግስት ድረ-ገጽ የተገኘ ፎቶ
ከሻባይት የመንግስት ድረ-ገጽ የተገኘ ፎቶ

በቱር ኤርትራ (Tour Eritrea) ቢሲክሌት ውድድር የኤርትራ ጋላቢዎች በአንደኝነት አጠናቀዋል።

የኢትዮጵያ እና የኬንያ አትሌቶች በተለያዩ ማራቶኖች ቀንቷቸዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:47 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG