በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“እናቴና ሁለት ወንድሞቼ ሰጥመው ሞተዋል” ታጅድን ሁሴን


እ.አ.አ ሚያዚያ 17 ቀን 2016 ጣሊያን ላምባዱሳ ደሴት ላይ ኤስ.ኦ.ኤስ መርከብ ደርሶ ሕይወታቸው የተርፉ
እ.አ.አ ሚያዚያ 17 ቀን 2016 ጣሊያን ላምባዱሳ ደሴት ላይ ኤስ.ኦ.ኤስ መርከብ ደርሶ ሕይወታቸው የተርፉ

ከግብፅ ወደ ጣልያን በመጓዝ ላይ እያለ በሰጠመው ጀልባ ላይ በአንድ ጊዜ ሦስት ቤተሰቦቹን አጥቷል። ሙሐዝ ሞሐመድ ባለቤቱንና የሁለት ወር ልጁን አጥቶ እሱ ተርፏል።

ከግብፅ ወደ ጣልያን የሚጓዙ ተሰዳጆችን የጫኑ ወደ አራት የሚጠጉ ጀልባዎች ሰጥመው እስከአሁን ከ400 ሰዎች በላይ መሞታቸውን እየተነገረ ነው። በእነዚህ ጀልባዎች ወደ 512 የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያንና ሶማሌያውያን ነበሩበት ተብሎ ይገመታል።

ተሰዳጆቹ እነዚህ ጀልባዎች ላይ የተሣፈሩት ከአሥራ ሦስት ቀናት በፊት እንደሆነ ከመስመጥ የተረፉትና የሟች ቤተሰቦች ይናገራሉ። ከተሳፈሩ ጀምሮ ድምፃቸው ጠፍቶ ቆይቶ የሞታቸውን ዜና ትናንትና ከትናንት በስቲያ ጀምሮ መስማታቸውን ይገልፃሉ፡፡

በስዊድን የሚገኘው ታጅድን ሁሴን እናቱን እና ሁለት ወንድሞቹን በዚህ አደጋ አጥቷል፡፡

ጽዮን ግርማ ዘገባ አላት።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ።

“እናቴና ሁለት ወንድሞቼ ሰጥመው ሞተዋል” ታጅድን ሁሴን
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:59 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG