በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ታላቁ የኅዳሴ ግድብ Great Reninssance

በኅዳሴ ላይ ድርድሩ እየተካሄደ ነው

ፎቶ ፋይል፦ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
ፎቶ ፋይል፦ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

ከሳምንታት በፊት በኅዳሴው ግድብ ዙሪያ ሲካሄድ የነበረው የግብፅ፣ የሱዳንና የኢትዮጵያ ውይይት ሲቋረጥ ሱዳን ተጨማሪ ጊዜ ከጠየቀች በኋላ የሦስቱ ሃገሮች የቴክኒክ ባለሞያዎች እንደገና ለድርድር መቀመጣቸው ተነገረ።

በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የባለሞያዎቹ ቡድኖች በነዚህ መነጋገሪያ ዋና ዋና ነጥቦች ምን እንደሚሆኑን አስረድተዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

በኅዳሴ ላይ ድርድሩ እየተካሄደ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:49 0:00


See all News Updates of the Day

ያለስምምነት በተጠናቀቀው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ግብጽ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌላት ተገለጸ

ያለስምምነት በተጠናቀቀው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ግብጽ የመቀጠል ፍላጎት እንደሌላት ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:53 0:00

በዐዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ቀናት የተካሔደው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አራተኛው ዙር ድርድር፣ ያለስምምነት እንደተጠናቀቀ፣ ትላንት ያስታወቁት ኢትዮጵያ እና ግብጽ፣ ለውጤት አልባነቱ አንዳቸው ሌላቸውን ወንጅለዋል፡፡

ግብጽ፥ “ውይይቱ ያልተሳካው ኢትዮጵያ ምንም ዐይነት ስምምነት ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመኾኗ ነው፤” ስትል፤ ኢትዮጵያም በበኩሏ፣ “የስምምነቱን መንገድ የዘጋችው ግብጽ ናት፤” ብላለች፡፡

በድርቅ ወቅት የሚኖረው የውኃ አያያዝ እና አለቃቀቅ፣ በድርድሩ ከፍተኛ ልዩነት የታየበት ጉዳይ እንደነበረ፣ የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ዶር. ስለሺ በቀለ ገልጸዋል፡፡

ግብጽ፣ “ከዚኽ በኋላ ድርድሩን የመቀጠል ፍላጎት የለኝም፤” እንዳለች የገለጹት አምባሳደር ስለሺ፣ የአፍሪካ ኅብረት ዳግም ወደ አደራዳሪነቱ ሊመለስ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን፣ በዐዲስ አበባ ለሦስት ቀናት ያካሔዱት የታላቁ የሕዳሴ ግድብ አራተኛ ዙር ድርድር፣ ትላንት ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ያለስምምነት መቋጨቱን ያስታወቁት ኢትዮጵያ እና ግብጽ፣ ለውጤት አልቦነቱ እርስ በርስ ተወነጃጅለዋል፡፡

ያለፉት አራት ዙር ድርድሮች የተካሔዱት፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤል-ሲሲ፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት እና አለቃቅ ዓመታዊ ክዋኔ ላይ፣ በአራት ወራት ውስጥ የመጨረሻ ስምምነት ላይ እንዲደረስ፣ በ2015 ዓ.ም. ሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ በተስማሙት መሠረት ነው፡፡

ይኹንና፣ በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ሥር ሲካሔድ የቆየው የግድቡ ድርድር፣ በሚያዚያ ወር 2013 ዓ.ም ላይ ከተቋረጠ በኋላ፣ በሦስቱ የተፋሰሱ ሀገራት መካከል፣ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ፣ በካይሮ እና በዐዲስ አበባ በተደረጉ የአራት ዙር ድርድሮች ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም፡፡

ለድርድሮቹ ፍሬያማ አለመኾን፣ ኹለቱ ሀገራት ባወጡት መግለጫ እርስ በርስ ተወቃቅሰዋል፡፡

የግብጽ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር፣ “ውይይቱ ያልተሳካው፥ ኢትዮጵያ ምንም ዐይነት ስምምነት ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመኾኗ ነው፤” ሲል ከሷል፡፡

ስምምነት ላይ ላለመደረሱ፣ ግብጽን ተጠያቂ የምታደርገው ኢትዮጵያም፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችው መግለጫ፣ “ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን አስተሳሰቧ በመቀጠል፣ ወደ መግባባት የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች፤” ስትል ወቅሳለች።

የሦስትዮሽ ድርድሩ ሲካሔድ የነበረው፣ 16 አንቀጾች ባሉት የጋራ መደራደሪያ ሰነድ ላይ በመመሥረት ሲኾን፣ ከፍተኛ ልዩነት የታየውም፣ በድርቅ ወቅት በሚኖረው የውኃ አያያዝ እና አለቃቀቅ ላይ ትኩረት በአደረገው አንቀጽ እንደኾነ፣ የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ስለሺ በቀለ (ዶር.) ድርድሩን አስመልክተው፣ ዛሬ ረቡዕ፣ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

ልናስኬድ የቻልነው እስከ ስድስተኛው ክፍል ነው ነው። ስድስተኛው ክፍል ላይ ደግሞ ልዩነት አለ፡፡ ይሄም የድርቅ ሁኔታን የሚያመላክተው የውሃ አያያዝና አለቃቅ ጉዳይ ነው፡፡”

“ልናስኬድ የቻልነው እስከ ስድስተኛው ክፍል ነው ነው። ስድስተኛው ክፍል ላይ ደግሞ ልዩነት አለ፡፡ ይሄም የድርቅ ሁኔታን የሚያመላክተው የውሃ አያያዝና አለቃቅ ጉዳይ ነው፡፡” ያሉት ዶር. ስለሺ በዚህ ላይ መግባባትና መቀራረብ ስላልተቻለ፣ ስድስት ሰዎች ያሉበት የባለሞያዎች ቡድን ጉዳዩን እንደገና እንዲመለከት ሁለት ሰዎች መወከላቸውን ተናግረዋል። ከኢትዮጵያ የተወከሉት ሰዎች ደግሞ ከሁለቱ ቀናት የሚኒስትሮቹ ስብሰባ አንድ ቀን ቀደም ብሎ መወያየታቸውን አምባሳደር ስለሺ ጨምረው አስረድተዋል።

ድርቅ በሚያጋጥምበት ወቅት በሚለቀቀው የውኃ መጠን ላይ፣ በተደራዳሪዎቹ ሀገራት መካከል የቁጥር ልዩነቶች መኖራቸውን፣ አምባሳደር ስለሺ ጠቅሰዋል፡፡ በውኃው የክፍፍል መጠን ላይ ስምምነት በሌለበት ኹኔታ፣ ከታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት በተቃራኒ ኢትዮጵያ፣ ቋሚ ቁጥር መቀመጥ የለበትም፤ የሚል አቋም እንዳላት፣ ዋና ተደራዳሪው አብራርተዋል፡፡

“ይሔን ቁጥር ስንሰጥ የኢትዮጵያን የወደፊት የመልማት ዕድል በሚገድብ መልኩ ሳይኾንን፣ የትብብር ስለሆነ ያንን ሊያስተካክል የሚችለው ሁላችንም የውሃ መብት ክፍፍላችን ሲታወቅ በዛ ስሜት እንሠራ።አን። እስከዛው መረጃ እየተለዋወጥን መቀጠል አለብን የሚል አቋም ነው ያለን፡፡ ይሔ ደግሞ ፍትሐዊነት ነው፡፡ ሕዳሴ ግድብን ብቻ ስለሠራን ልማት አናቆምም፡፡ ከላይ የምንሠራቸው ግድቦች የውሃ ጉዳይ በኛ ድርሻ ውስጥ የሚካተት ነው፡፡ አሁን ያ ድርሻ የተቀመጠ ስላልሆነ በድርድር ውስጥ ለዚህ ዓይነት ችግር አጋልጦናል” ያሉት አምባሳደር ስለሺ ኢትዮጵያ፣ “ግትር አቋም ይዛለች፤” በሚል ግብጽ የምታቀርበውን ውንጀላም አስተባብለዋል፡፡

“ድርቅ ቢከሰት፣ ተፈጥሮ ከምትሰጠው በላይ ውሃ ጨምሮ ከመስጠት ሌላ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡ ከዛ በላይ መፍትሔ የለም፤ ቢኖር እነሱም ያቀርቡት ነበር፡፡” ያሉት ዋና ተደራዳሪው፤ “የሚፈለገውን መፍትሔ አስቀምጠናል፡፡ ነገር ግን እኛ ሀገር ላይ ጉዳት በሚያስከትል፣ ወይም ቀደም ሲል አለን በሚሉት የውሃ ኮታ መሰረት፣ ውሃውን ሙሉ በሙሉ ከተካፈሉ በኋላ ኢትዮጵያ ይሄን አረጋግጣ እንድትሰጣቸው የመፈለግ አካሔድ የትም ሊደርስ አይችልም፡፡ ትክክለኛም አይደለም፤ እኛ ሀገር ሊያሰቅል ይችላል፡፡ የትም ሀገር ቢሆን ሃብቱን ሙሉ በሙሉ አሳልፎ አይሰጥም፡፡ እንደላይኛው ተፋሰስ እኛ ብቻችንን እንጠቀም አላልንም፡፡ ተካፍለን አብረን እንልማ የሚል አቋም ነው ያለን፡፡” ብለዋል።

“ኢትዮጵያ በድርድር ሽፋን፣ በኣባይ ወንዝ ላይ ከቁጥጥር ውጭ የኾነ ባለቤትነት እንዳላት፣ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ይኹንታ ለማግኘት ብቻ መደራደርን መርጣለች፤” ያለው የግብጽ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር፣ “ግብጽ በዓለም አቀፍ ቻርተሮች እና ስምምነቶች መሠረት፣ በውኃዋ እና ብሔራዊ ደኅንነቷ ላይ ጉዳት በሚደርስበት ጊዜ ጥቅሟን የመከላከል መብቷ የተጠበቀ ነው፤” ሲልም አስጠንቅቋል፡፡

“ኢትዮጵያ በድርድር ሽፋን፣ በኣባይ ወንዝ ላይ ከቁጥጥር ውጭ የኾነ ባለቤትነት እንዳላት፣ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ይኹንታ ለማግኘት ብቻ መደራደርን መርጣለች፤”

ኢትዮጵያ በበኩሏ፣ በግድቡ ላይ የሚደረገው ድርድር፣ በሦስቱ ሀገራት መካከል መተማመን ለመፍጠር ያለመ እንጂ፣ “በዓባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ የኢትዮጵያን መብቶች ለማስነጠቅ አይደለም፤” ብሏል። የግብጽ መግለጫ፣ “የተባበሩት መንግሥታትን ቻርተር እና የአፍሪካ ኅብረትን ድንጋጌ የሚፃረር” እንደኾነም ሚኒስቴሩ ተችቷል፡፡ ኢትዮጵያ፣ የውኃ ሀብቷን፥ “ፍትሐዊ እና ምክንያታዊ በኾነ መንገድ፣ የአኹንና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት መጠቀሟን ትቀጥላለች፤” ሲልም አክሏል፡፡

አምባሳደር ስለሺ በቀለ በዛሬው መግለጫቸው፣ በድርድሩ ላይ ግብጽ፣ “ነባሩን የቅኝ ግዛት ዘመን የውኃ ክፍፍል የሚያንጸባርቅ” ሐሳብ በተደጋጋሚ ከማንሣቷም በላይ፣ “ቀጣይ ድርድር የማድረግ ፍላጎት እንደሌላትም ይፋ አድርጋለች፤” ብለዋል፡፡ ይኹንና ቀጣይ የድርድሩ ሒደት፣ በአፍሪካ ኅብረት መሪነት ሊቀጥል እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ አጠቃላይ የግንባታ መጠን፣ ከ94 በመቶ በላይ መድረሱን የገለጹት ዋና ተደራዳሪው አምባሳደር ስለሺ በቀለ(ዶር.)፣ ተጨማሪ አምስት ተርባይኖችም፣ በዚኽ ዓመት ኀይል ማመንጨት ይጀምራሉ፤ ሲሉ አክለው ገልጸዋል፡፡

የሕዳሴው ግድብ ላይ ድርድር ዛሬ ተጀምሯል

ፎቶ ፋይል - የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል - የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ

ግብጽ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን፣ ኢትዮጵያ እየገነባች ባለችው የህዳሴ ግድብ ላይ የሚያደርጉትን አራተኛ ዙር ድርድር ዛሬ አዲስ አበባ ላይ መጀመራቸውን ኢትዮጵያን የሚወክሉት ዋና ተደራዳሪ አምባሳደር ስለሺ በቀለ በ X ማኅበራዊ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል።

ሶስቱ ወገኖች ባለፈው መስከረም አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ሶስተኛ ዙር ድርድር ካለ ውጤት ተበትኖ እንደነበር ይታወሳል።

ድርድሮቹ በመደረግ ላይ ያሉት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እና የግብጹ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደል ፋታህ አል ሲሲ፣ በኢትዮጵያ እየተገነባ ባለው የህዳሴ ግድብ ጉዳይ፣ በአራት ወራት ውስጥ ስምምነት ላይ እንደሚደርሱ ባለፈው ሐምሌ ማስታወቃቸውን መሠረት አድርጎ ነው።

አራተኛው እና በአዲስ አበባ በመቀጠል ላይ ያለው ድርድር፣ ከዚህ ቀደም በተደረጉ ድርድሮች እና ትናንት እሁድ በቴክኒካዊ ቡድኑ በተደረጉ ውይይቶች ላይ እንደሚመሠረት አምባሳደር ስለሺ ጨምረው አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ የምትመራው ግድቡን በተመለከተ እ.አ.አ 2015 በተደነገገው የመርህ ስምምነት እንዲሁም በጋራ እና በእኩልነት ላይ በተመሠረተ አጠቃቀም መሆኑንም አምባሳደሩ ገልጸዋል።

4.6 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው ግድብ ፍላጎቷን ከግምት ውስጥ የማያስገባ ከሆነ፣ የናይልን ወንዝ ለግብርና እና 100 ሚሊዮን ለሚሆን ሕዝቧ የውሃ ፍጆታ የምትጠቀመው ግብጽ ትልቅ ስጋት እንደሚሆንባት ስትገልጽ ቆይታለች

አብዛኛው የሀገሪቱ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ባለመሆኑ፣ ግድቡ አስፈላጊ እንደሆነ ኢትዮጵያ በበኩሏ ትገልጻለች፡፡

አራተኛውን ዙር የግድቡ ሙሌት ባለፈው 2015 መጨረሻ ላይ እንዳጠናቀቀች ኢትዮጵያ ማስታወቋ አይዘነጋም።

የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል

የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:59 0:00

በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጉዳይ፣ በዐዲስ አበባ የተደረገው ውይይት ያለስምምነት ለመጠናቀቁ፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ አንዳቸው ሌላቸውን ወቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ በድርድሩ የሚሳተፈው “የግብጽ ወገን፣ የ2015ቱን የመርሖዎች ስምምነት የማፍረስ አቋሙን ገፍቶበታል፤” ብሏል።

የግብጽ የመስኖ እና የውኃ ሚኒስቴር ደግሞ፣ ኢትዮጵያ፣ “ምንም ዐይነት ስምምነትን ትቃወማለች፤” ሲል ወቅሷል።

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚህ ሹክሪ፣ ለቪኦኤ በሰጡት አስተያየት፣ ለድርድሩ መጓተት ኢትዮጵያ የምትከተለውን መንገድ ተጠያቂ አድርገዋል።

በሌላ በኩል፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን አባል ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ድርድሩ ውጤታማ ያልኾነው በግብጽ ምክንያት እንደኾነ ገልጸዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ግብጽ የሕዳሴው ግድቡን አራተኛ ሙሌት “ሕገ ወጥ” ስትል አወገዘች

ፎቶ ፋይል፦ የኢትዮጵያ፣ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ
ፎቶ ፋይል፦ የኢትዮጵያ፣ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ

ኢትዮጵያ፣ የታላቁ የሕዳሴ ግድብን አራተኛ ሙሌት እንዳጠናቀቀች ስታስታውቅ፣ ግብጽ በበኩሏ፣ “ሕገ ወጥ ነው” ስትል አወገዘች፡፡

ሚኒስቴሩ፣ ትላንት እሑድ፣ ጳጉሜን 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ዐዲስ አበባ፣ የግድቡን ሙሌት ለማጠናቀቅ የወሰደችው “የተናጠል” ውሳኔ፣ “እ.ኤ.አ በ2021 ዓ.ም ተቋርጦ ባለፈው ወር ዳግም የተጀመረውን የሦስትዮሽ ድርድር ወደ ጎን የተወ ነው፤” ማለቱን አሶሺዬትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ “በውስጥ ፈተና፣ በውጭ ጫና ነበረብን። ከፈጣሪ ጋራ የመጣውን ሁሉ ተቋቁመን ለዚኽ ደርሰናል፤” ሲሉ፣ የሕዳሴ ግድቡ አራተኛ ሙሌት እንደተጠናቀቀ፣ ትላንት እሑድ፣ በፌስቡክ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በካርቱም በሦስቱ ሀገራት የተፈረመው የ2015 የመርሖዎች ስምምነት፣ ሦስቱ ሀገራት፥ በሕዳሴ ግድቡ ሙሌት እና የመተዳደሪያ ደንቦች ላይ መስማማት እንዳለባቸው የደነገገውን አስታውሷል፡፡

አያይዞም፣ “የኢትዮጵያ የአንድ ወገን አካሔድ፣ በዓለም አቀፍ ሕግ የተደነገጉ የተፋሰሱን የታችኛው ሀገራት መብት እና ጥቅም፣ እንዲሁም የውኃ ደኅንነታቸውን ወደ ጎን የተወ ነው፤” ሲልም ተችቷል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከግብጽ በኩል ስለቀረበው ወቀሳ እስከ አሁን በይፋ የሰጠው ምላሽ የለም፡፡

ኾኖም፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን መሪና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ(ዶር.)፣ ባለፉት አራት ዓመታት፣ የውኃ ሙሌት ሥራውን ለማከናወን የሚያስችል በቂ የዝናም መጠን እንደተገኘና በታችኛው ተፋሰስ ሀገራትም ላይ ምንም ዐይነት ጉዳት በማያደርስ መልኩ እንደተከናወነ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የግድቡ የውኃ ሙሌት፣ ከግንባታው ሒደት ጋራ ጎን ለጎን እንደሚከናወን የምትገልጸው ኢትዮጵያ፣ ይህም፣ ሦስቱ ሀገራት በተፈራረሙት የመርሖዎች ስምምነት መሠረት እንደሚፈጸም በተደጋጋሚ አስታውቃለች፡፡

በአፍሪካ ኅብረት አመቻችነት የሚካሔደው የሦስትዮሽ ድርድር፣ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 2021 ከተቋረጠ በኋላ፣ በነሐሴ ወር በካይሮ አስተናጋጅነት የተካሔደው ውይይትም፣ ተጨባጭ ውጤት እንዳላመጣ ግብጽ ይፋ አድርጋለች፡፡ ለዚኽም “ግትር አቋም ይዛለች፤” ያለቻትን ኢትዮጵያን ተጠያቂ አድርጋለች፡፡

ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለ ግብጽ ወቀሳ እና ትችት ጥያቄ የተነሣላቸው፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም፣ ውድቅ አድርገውታል፡፡

ኢትዮጵያ፣ በግድቡ ጉዳይ ሦስቱንም ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ እንደኾነች የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ በካይሮው ውይይት ላይ፣ “ግብጽስ ከቀድሞው የተለየ ምን አቋም አራምዳለች?” በሚል መጠየቅ እንዳለባት አመልክተዋል፡፡

በአወዛጋቢው የሕዳሴ ግድብ ውኃ ሙሌት ጉዳይ፣ ቀጣይ ዙር የሦስትዮሽ ውይይት፣ በዐዲስ አበባ እንደሚካሔድ ይጠበቃል፡፡

ሀመር በኅዳሴ ጉዳይ አውሮፓ ናቸው

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሀመር በዚህ ሳምንት ወደ ስቶክሆልም እና ብራስልስ ተጉዘው በኅዳሴ ግድብ እና እንዲሁም ኢትዮጵያ እና ሱዳን ውስጥ እየተካሄዱ ባሉት ግጭቶች ዙሪያ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የስቶክሆልሙ ዓለም አቀፍ የውሃ ጉዳይ ተቋም በሚያስተናግደው የዓለም የውሃ ሳምንት ጉባዔ ላይ የሚካፈሉት አምባሳደር ማይክ የስቶክሆልም ዓለም አቀፍ የሰላም እና ምርምር ተቋም በሚያስተናግደው ውይይት ላይም እንደሚካፈሉ ተመልክቷል፡፡

ሀመር የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዋናው የዩናይትድ ስቴትስ መልዕክተኛ እንደመሆናቸው የውሃ አያያዝ፣ አጠቃቀም እና ተደራሽነትነት የሚመለከቱ ሥምምነቶች ለአፍሪካ ቀንድ ጸጥታ እና መረጋጋት ሊያበረክቱ ስለሚችሉት አስተዋጻኦ እንደሚወያዩ ተገልጿል፡፡ በመቀጠል ወደብረሰልስ በማቅናት ኢትዮጵያን እና ሱዳንን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከአውሮፓ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር እንደሚወያዩ ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡

አምባሳደር ሀመር በኢትዮጵያ ጉዳይ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች በውይይት ለመፍታት ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ሕብረት እንዴት ሊደግፉ እንደሚችሉ፤ በተጨማሪም ለሰላማዊ ዜጎች በሚደረግ ጥበቃ አስፈላጊነት ዙሪያም እንደሚወያዩ ተገልጧል።

ልዩ መልዕክተኛው ከአውሮፓ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር ሚያደርጓቸው ውይይቶች የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ለማስቆም ምክኒያት የሆነው ሥምምነት በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እና በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን በሙሉ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሰላም፣ ፍትህ እና ተጠያቂነትን ለማስፈን በሚሰጡት ድጋፍ ዙሪያም ይመክራሉ ተብሏል።

አምባሳደር ሀመር በሱዳኑ ግጭት የአፈሙዞች ላንቃ እንዲዘጋ፤ ተጠያቂነትን ለማስከበር እና ዲሞክራሲያዊ የሲቪል አስተዳደር ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ የተያዙ አህጉራዊ እና አለምአቀፋዊ ጥረቶች ዙሪያም ይወያያሉ። ለክልሉ የሚሰጠውን ሰብአዊ ድጋፍ ለማጠናከር የተያዘው ሥራ ማቀላጠፉ እንደሚቀጥልም መግለጫው ጠቅሷል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG