በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ታላቁ የኅዳሴ ግድብ Great Reninssance

በኅዳሴ ላይ ድርድሩ እየተካሄደ ነው

ፎቶ ፋይል፦ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

ከሳምንታት በፊት በኅዳሴው ግድብ ዙሪያ ሲካሄድ የነበረው የግብፅ፣ የሱዳንና የኢትዮጵያ ውይይት ሲቋረጥ ሱዳን ተጨማሪ ጊዜ ከጠየቀች በኋላ የሦስቱ ሃገሮች የቴክኒክ ባለሞያዎች እንደገና ለድርድር መቀመጣቸው ተነገረ።

በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የባለሞያዎቹ ቡድኖች በነዚህ መነጋገሪያ ዋና ዋና ነጥቦች ምን እንደሚሆኑን አስረድተዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

በኅዳሴ ላይ ድርድሩ እየተካሄደ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:49 0:00


See all News Updates of the Day

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:33 0:00

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ

ፎቶ ፋይል፦ የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ

የውሃ ሙሌቱ መጠናቀቅ “የዲፕሎማሲውን በር በሰፊው የሚከፍት ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጉባ ተራራዎች ስር፣ መጋቢት 24/2003 ዓ.ም የመሰረት ድንጋዩ ከተቀመጠለት ጊዜ ጀምሮ ሦስት መሪዎች የተፈራረቁበት እና አሁንም በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ሙሌት መጠናቀቁ ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡

የግድቡ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቆ ውሃው ከዛሬ ነሐሴ 6 ጀምሮ በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ መጀመሩን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሥፍራው አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ የጋራ ሀብታቸው የሆነውን የዓባይን ወንዝ በትብብር ሊጠቀሙ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የግድቡ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት የተከናወነው፣ በኢትዮጵያ፣ በግብጽ እና ሱዳን መካከል ያለው አለመግባባት ተባብሶ በቀጠለበት ወቅት ነው፡፡

የግድቡ እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ በአባይ ተፋሰስ የግርጌ ሃገሮች መካከል ትብብር እንዲኖር “የዲፕሎማሲውን በር በሰፊው የሚከፍት ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ተናግረዋል፡፡ ግድቡ ኃይል ከማመንጨት ያለፈ ሀገራዊ ትርጉም እንዳለውም ያነሱት ፕሬዚዳንቷ፣ ይሄውም “ኢትዮጵያውያን ከተባበርን ለዚህ መድረስ እንችላለን የሚል ነው" ብለዋል፡፡

3ኛውን ዙር የግድቡን የውሃ ሙሌት በመቃወም ግብጽ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ለመንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ደብዳቤ ያስገባች ሲሆን “በግብፅ ጥቅም ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም ጉልህ ጉዳት ኢትዮጵያ ሙሉ ኃላፊነት ትወስዳለች” ስትል በደብዳቤዋ ገልጻለች።

የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:33 0:00

ሥምምነት የራቀው እና በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ሲካሔድ የነበረው የሦስትዮሽ ድርድርም ከተቋረጠ ቆይቷል፡፡ ሀገራቱ ለመጨረሻ ጊዜ ለድርድር የተቀመጡት በሚያዝያ ወር 2013 ዓ.ም ነው፡፡

ኢትዮጵያ በግድቡ የውሃ ሙሌት እና ከግድቡ በሚለቀቀው የውኃ መጠን ላይ አስገዳጅ ስምምነት እንድትፈርም የሚፈልጉት ግብጽና ሱዳን እስካሁን ለተካሔዱት ድርድሮች አለመሳካት ግትር አቋም ይዛለች በማለት ኢትዮጵያን ተጠያቂ ያደርጋሉ፡፡ በተቃራኒው ግትር አቋም የያዙት ግብጽና ሱዳን መሆናቸውን የምትገልጸው ኢትዮጵያ ለድርድሩ ውጤታማ አለመሆን ጣቷን የምትቀስረው በሁለቱ ሀገራት ላይ ነው፡፡

የግድቡን ሦስተኛ ዙር ሙሌት በማስመልከት ንግግር ያደረጉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ ወቅታዊው የግድቡ ሁኔታ የሁለቱ ሀገራት ክስ ሐሰት መሆኑን እንደሚያጸባርቅ አመለክተዋል፡፡

በግድቡ ጉዳይ በሦስቱ ሀገራት መሃከል ያለው ልዩነት በንግግር እንዲፈታ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በመጠየቅ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በቅርቡ በካይሮ እና በአዲስ አበባ ጉብኝት ያደረጉት የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመርም ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ እና የኢትዮጵያ የልማት ፍላጎት በሰፊው መረዳታቸውን ገልጸው፣ በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ሥር በሚካሔደው የዲፕሎማሲ ጥረት፣ ሁሉንም የተፋሰሱን ሀገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ ሥምምነት ላይ መድረስ ይቻላል ብለዋል።

በ2012 የክረምት ወቅት ላይ 4.9 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በመያዝ ሙሊቱ የተጀመረው የኅዳሴው ግድብ፣ አሁን በሦስተኛው ዙር የያዘው የውኃ መጠን 22 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ግድቡ ሙሉ ለሙሉ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የሚይዘው የውሃ መጠን 74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ አጠቃላይ የማመንጨት አቅሙ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት ነው።

ከኅዳሴ ግድቡ 13 የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች መካከል፣ 9ኛው ዩኒት ትናንት ሥራ የጀመረ ሲሆን 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ በሙሉ አቅሙ የማመንጨት ደረጃ ላይ እስኪደርስ አሁን ላይ እስከ 270 ሜጋ ዋት እንደሚያመነጭ ተገልጿል፡፡ ተመሳሳይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው 10ኛው ዩኒት ባለፈው የካቲት 13/2014 ዓ.ም ሥራ መጀመሩ ይታወሳል፡፡

የግድቡ አጠቃላይ የግምባታ አፈጻጸም 83 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን ያስታወቁት ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፣ በ 2 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የግድቡ ግምባታ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡

ከአፍሪካ ትልቁ የውኃ ኃይል ማመንጫ የሆው የኅዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ 145 ሜትር ከፍታ እና 1,780 ሜትር ርዝማኔ ይኖረዋል፡፡ ውሃው ከግድቡ ወደ ኋላ 240 ኪሎ ሜትር ድረስ እንደሚያርፍም ይጠበቃል፡፡

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:00 0:00

ሁለተኛው እና 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኅዳሴ ግድብ ተርባይን የኤሌክትሪከ ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ዛሬ ይፋ ተደረገ። አጠቃላይ ግንባታው በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።

ሦስተኛው ሙሌት በሂደት ላይ መሆኑን የገለጹት የኅዳሴ ግድቡ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የግድቡን ሁለተኛ ዩኒት የኤሌክትሪከ ኃይል ማመንጫ ሥራ ያስጀመረችው ከአባይ ተፋሰስ የግርጌ ሃገሮች ማለትም ግብጽ እና ሱዳን ጋር ያላት አለመግባባት ተባብሶ በቀጠለበት ወቅት ነው፡፡

ኢትዮጵያ ከእነዚህ ሃገሮች ጋራ ስምምነት ላይ ሳትደርስ ኅዳሴ ግድብን ለሦስተኛ ጊዜ መሙላት ልትጀምር ነው ስትል ግብፅ በቅርቡ ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ተቃውሞ ማቅረቧን ይታወሳል።

በአፍሪካ አቻ የሌለው ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ይሆናል የተባለው ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ በተለይ በኢትዮጵያና በሁለቱ የግርጌ ሃገሮች መካከል የውጥረትና የንትርክ ሰበብ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።

ዛሬ ሁለተኛውን የኅዳሴ ግድብ ተርባይ የኤሌክትሪከ ኃይል ማመንጫ መርቀው የከፈቱት

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀገራቸው የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት የመጉዳት ፍላጎት እንደሌላት ገልጸው፣ ከውይይት ውጭ የሚወሰድ እርምጃ ማንንም እንደማያዋጣ ተናግረዋል።

የዛሬ አሥራ አንድ ዓመት የተጀመረው ከአራት ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው የኅዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ 5000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል።

/ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ

የኅዳሴ ግድብ ግንባታ በሁለት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:00 0:00

ግብፅ የኅዳሴ ግድብን ሦስተኛ ሙሌት ተቃወመች

ፎቶ ፋይል፦ ኅዳሴ ግድብ

ኢትዮጵያ ከዓባይ ተፋሰስ የግርጌ ሃገሮች ጋር ስምምነት ላይ ስትደርስ ኅዳሴ ግድብን ለሦስተኛ ጊዜ መሙላት ልትጀምር ነው ስትል ግብፅ ለተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ተቃውሞ ማቅረቧን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ።

በአፍሪካ አቻ የሌለው ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ይሆናል የተባለው ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ በተለይ በኢትዮጵያና በሁለቱ የግርጌ ሃገሮች መካከል የውጥረትና የንትርክ ሰበብ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።

ኢትዮጵያ በዚህ ክረምት ግድቡን መሙላት እንደምትቀጥል የሚያሳውቅ ድብዳቤ ባለፈው ሣምንት ማክሰኞ ለግብፅ መላኳንና ካይሮም መልዕክቱ እንደደረሳት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መናገሩን ግብፅም የተቃውሞ አቤቱታዋን ይዛ ወደ መንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታ ምክር ቤት መሄዷን ኤኤፍፒ አክሎ ጠቁሟል።

የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማከልም “ግብፅ ብሄራዊ ደኅንነቷን ለማስከበርና ወደፊት ኢትዮጵያ በተናጠል በምትወስዳቸው እርምጃዎች ምክንያት የሚመጡ አደጋዎችን ለመከላከል ህጋዊ መብቷን ተጠቅማ አስፈላጊውን እርምጃ ትወስዳለች” ብሏል።

የዛሬ አሥራ አንድ ዓመት የተጀመረው ከአራት ቢሊዮን ዶላር የሚፈጀው የኅዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ 5000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል።

ዛሬ፤ ሰኞ ከግብፅ ባለሥልጣናት ጋር የተነጋገሩትና ባለፈው ዓርብ ኢትዮጵያ የነበሩት የዩናይትድ ስቴትስ አዲሱ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሃመር የአሁን ጉብኝት ዝርዝር ለጊዜው ባይገለፅም ውይይቶቻቸው አጨቃጫቂውን የኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ሳይጨምር እንደማይቀር ተነግሯል።

ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG