በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ስደት በአረብ ሀገራት


ፋይል-ፎቶ ኢትዮጵያውያን ከስደት መልስ
ፋይል-ፎቶ ኢትዮጵያውያን ከስደት መልስ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በስራ ላይ የሚገኘው የዲፕሎማሲ መምሪያ በ2015 መጨረሻ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሃገራቸውን ጥለው በጅቡቲ ወደብ በሶማሊያና በሱዳን አቋርጠው ወደ የመንና መካከለኛው ምስራቅ አሁንም እየተሰደዱ እንደሚገኙ አስታውቋል።

በዚህ ፈታኝ ጉዞ ውስጥ ወጣቶች እንደወጡ ይቀራሉ፣ ከሞት የተረፉትም ለዘረፋ፣ለብዝበዛ ይጋለጣሉ፣ ሴቶችና ህፃናት ይደፈራሉ ለወሲብ ንግድም ይጋለጣሉ። ታዲያ የመንገዱን መከራ ሲያልፉ በገቡበት ሃገር ደግሞ ሌላ መከራ ይጠብቃቸዋል። ሕጋዊ የመኖሪያና የስራ ፈቃድ የላቸውም፤ ለማግኘትም መንገዱ በጣም ጠባብ ነው።

በእግርና በጀልባ ለወራቶች ተጉዘው ሳውድ አረቢያ ከገቡት ጥቂት ወጣቶች ውስጥ አንዱ ነው ሰኢድ። በኢትዮጵያ ሳለ ተማሪ ነበር። የራሱንና የቤተሰቡን ህይወት ለመለወጥ ፈለገና፤ ወደ ውጭ ተመለከተ፤ ወደ መካከለኛው ምስራቅ። የአረብ ሀገር ጉዞ ፈተናውን ጨረስኩ ሲል በሳውዲ አረቢያ ሰርቶ ለማደር የሚያስችል ፈቃድ ስለሌለው አሁን የየዕለት ፈተና ውስጥ ይገኛል። ስላለበት ሁኔታ ለመስታወት አራጋው እንዲህ አጫውቷታል።

ከበታች ያለውን የድምፅ ምልክት በመጫን ያዳምጡ።

ስደት ወደ አረብ ሀገራት
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:54 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG