በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኦሮሚያ ክልልና በአዲስ አበባ ተቃውሞ መቀጠሉ ተጠቆመ


የኦሮሚያ ክልል ካርታ /ምንጭ - ተመድ/
የኦሮሚያ ክልል ካርታ /ምንጭ - ተመድ/

በደብረዘይቱ የኢሬቻ በዓል ወቅት በሰው ሕይወት ላይ የደረሰውን ጥፋት ተከትሎ ዛሬም በአዲስ አበባና በሌሎች የሃገሪቱ አካባቢዎች ተቃውሞ ተካሂዷል።

በሰንዳፋ ከ160 በላይ ሰዎች ተይዘው ወደ ሆለታ መሄዳቸውንና አንድ የ 15 ዓመት ልጅ በፀጥታ ሹሙ መገደሉን ነዋሪዎች ሲናገሩ፥ ባለሥልጣኑ ግን አስተባብለዋል።

በወለጋ ጊምቢ ከተማ የመንግሥቱ ኃይሎች ሕዝቡ እንዳይይንቀሳቀስ አግደዋል። ወጣቱ ከተማዋን ለቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል ተብሏል።

በከተማዋ መደብሮች የሚዘጉ፥ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ያቋረጡ ፀረ-ሰላም ኃይሎች አሉ ሲሉ የጊምቢ ፖሊስ አዛዥ ተናግረዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

በኦሮሚያ ክልልና በአዲስ አበባ ተቃውሞ መቀጠሉ ተጠቆመ
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:55 0:00

XS
SM
MD
LG