በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች አካባቢ የነበረው ድባብ ሰላማዊ እንደነበር አንዳንዶቹ ድምጽ ሰጪዎች ሲናገሩ ብዛት ያለው ወታደር አይተናል ያሉም አሉ።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ዛሬ ዓርብ ጅቡቲ ውስጥ ፕሬዚደንታዊ ምርጭ እየተካሄደ ነው። ቁጥራቸው ወደ 190,000 የሚጠጋ ድምጽ ሰጪዎች ከቀረቡት ስድስት ተፎካካሪዎች መሃል ይመርጣሉ።
A voté !#Djibouti #IOG2016 #DjiboutiAvantTout pic.twitter.com/ONRt8EGxSc
— Ismail Omar Guelleh (@IsmailOguelleh) April 8, 2016
የሃገሪቱ ፕሬዝደንት ጌሌ ዛሬ ጠዋት ጅቡቲ ከተማ ድምጽ የሰጡ ሲሆን “ድምጼን በመስጠት ብሄራዊ ግዴታዬን ተወጥቻለሁ። ድምጼን የሰጠሁት ለራሴ ነው። አብዛኛው ህዝብም ይህንኑ እንደሚያደርግ ተስፋ አለኝ“ ብለዋል።
በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች አካባቢ የነበረው ድባብ ሰላማዊ እንደነበር አንዳንዶቹ ድምጽ ሰጪዎች ሲናገሩ ብዛት ያለው ወታደር አይተናል ያሉም አሉ።
ተቃዋሚ መሪዎች ሂደቱ ተዛብቷል ሲሉ ከወዲሁ ሲያማርሩ ቆይተዋል። መንግስቱ ሁለት ተወካዮቻችንን ከድምጽ መስጫ ጣቢያ አስወጥቶብናል ሲሉ ሁለት ተቃዋሚ መሪዎች ከሰዋል።
እ.አ.አ. ከ1999 ጀምረው ስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዚደንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ እንደሚያሸንፉ በብዙዎች የሚጠበቅ ሲሆን የምርጫው ውጤት ነገ ቅዳሜ ጡዋት ይፋ እንደሚሆን ተገልጿል።
Your browser doesn’t support HTML5