በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጂቡቲ ሀይማኖታዊ ኩነት ላይ በከፈተ ተኩስ በርካታ ሰዎች ሞተዋል


የጂቡቲ የጸጥታ ሃይሎች ዛሬ በአንድ ሀይማኖታዊ ኩነት ላይ በከፈቱት ተኩስ በርካታ ሰዎች ሞተዋል ሲሉ እማኞች ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ የሶማልኛ አገልግሎት ተናግረዋል።

የጸጥታ ሃይሎቹ ሃይማኖታዊው ኩነት እንዳይካሄድ ያስጠነቀቁ ቢሆንም አዘጋጆቹ ችላ እንዳሉትና ሟቹ ሃይማኖታዊ መሪ ሼኽ ዮኒስ ሙሴን ለማሰብ እንደተሰባሰቡ ምንጮች ጠቁመዋል።

የጸጥታ ሃይሎቹ የተሰባሰቡትን ሰዎች ለመበተን ሞክረው እንደነበር ጂቡቲ ያሉት ጋዜጠኞችና እማኞች ተናግረዋል። በሀገሪቱ ያለ የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ዘጋቢ ቢያንስ ሁለት ሰዎች እንደተገድሉ ዘግቧል። ሌሎች ምንጮች ደግሞ ከዛ የበዛ ነው ይላሉ።

የዜና ዘገባውን ለማዳመጥ የድምጽ ፋይሉን ይጫኑ።

በጂቡቲ ሀይማኖታዊ ኩነት ላይ በከፈተ ተኩስ በርካታ ሰዎች ሞተዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:00:37 0:00

XS
SM
MD
LG