በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሞቅዲሾ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 3 የፖሊስ መኮንኖች ተገድለዋል


በሞቅዲሾ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 3 የፖሊስ መኮንኖች ተገድለዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:00:49 0:00

በሞቅዲሾ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 3 የፖሊስ መኮንኖች ተገድለዋል

የሞቅዲሾ ፖሊስ ዋና ኮሚሽነር አሊ ሀርሲ ባሬ እንደገለጹት፣ በፍንዳታው ክፉኛ የቆሰለው አሽከርካሪ ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር ውሏልኝ።

ሶማልያ ዋና ከተማ ሞቅዲሾ ውስጥ በሚገኝ አንድ የፖሊስ ጣቢያ አቅራቢያ ዛሬ ረቡዕ በደረሰ የመኪና ውስጥ ቦምብ ፍንዳታ፣ ቢያንስ 3 የፖሊስ መኮንኖች መገደላቸው ተሰማ።

የሞቅዲሾ ፖሊስ ዋና ኮሚሽነር አሊ ሀርሲ ባሬ እንደገለጹት፣ በፍንዳታው ክፉኛ የቆሰለው አሽከርካሪ ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር ውሏልኝ።

ፖሊስ ምርመራ እያካሄደ መሆኑንም ባሬ ጠቅሰዋል።

አል-ሻባብ የውጪ ዜጎች የሆኑ ተዋጊዎችን ከሶማልያ አባረርን ይላሉ

በሌላ በኩል ደግሞ፤ የአል-ሻባብ ነውጠኞች፣ የውጪ ዜጎች የሆኑ ተዋጊዎችን ከሶማልያዋ አውደግሌ ከተማ ዛሬ ረቡዕ ማለዳ አባረናቸዋል ሲሉ አስታወቁ።

አንዳለስ (Andalus) የሚባለው የአል-ሻባብ ራድዮ ይፋ ባደረገው ዘገባ፣ ከሄሊኮፕተር የወረዱትና ወደ ከተማዋ ሊዘልቁ ያቀዱት ልዩ ኃይሎች፣ በአል-ሻባብ ሚሊሽያዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶባቸው ሊመለሱ ተገደዋል ይላል።

ሄሊኮፕተሯ ከማረፏ በፊት ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የገለጹት የአል-ሻባብ ሚሊሻዎች፣ ከመካከላቸው አንድ ሰው መገደሉንም ጨምረው ተናግረዋል።

XS
SM
MD
LG