በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የተቃውሞ ሰልፎች በኦሮሚያና በውጭ አገሮች ከተሞች፥ ግጭቶችና አማራጮች


በኦሮምያ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ትምሕርት ቤቶች ተማሪዎች መሰንበቻውን በማካሄድ ላይ ያሏቸው የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ዛሬም ቀጥለዋል።

በኦሮምያ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ትምሕርት ቤቶች ተማሪዎች መሰንበቻውን በማካሄድ ላይ ያሏቸው የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ዛሬም ቀጥለዋል።

በዛሬዎቹ ሰልፎች ወቅት በአንዳንድ አካባቢዎች የተገደሉ ሰዎች መኖራቸውን ለአሜሪካ ድምጽ የተናገሩ አንዳንድ የአካባቢዎቹ ነዋሪዎችና በአካባቢዎቹ የሚንቀሳቀሰው የኦሮሞ ፌድራሊት ኮንግሬስ አመራሮች ተናግረዋል።

የአገራችን ሕገ መንግስት በግልጽ እንዳስቀመጠው ክልሎች የራሳቸውን ሕግ ያወጣሉ። ይሄ ሕግ የወጣው ኦሮምያ ክልል ከተሞች ላይ ነው እንጂ ከማስተር ፕላኑ ጋር ግንኙነት የለውም።
የኦሮምያ ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ንጉሴ መንግስቱ

በተያያዘ ሌላ ዜና በተለያዩ አካባቢዎች “በመንግስት ኃይሎች ተወሰዱ፤” ያሏቸውን የሰው ሕይወት እስከ ማጥፋት የደረሱ እርምጃዎች በመቃወም በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ በአሸባሪነት የሚፈርጃቸውን ሁለት የተቃዋሚ ፓርቲዎች፥ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ’ን) እና ግንቦት ሰባት’ን ተቃውሞዎቹን በመቀስቀስ ይወነጅላል።

በሰላም የሚካሄዱ ሰላማዊ ሰልፎችን፤ ሰላማዊ ጥያቄን ማጠልሸት ለአገሪቷም ሆነ ለመንግስት አይጠቅምም። ሰው ሊገደል ሊደበደብ አይገባም ጥያቄ ስለጠየቀ። የሰለጠነው መንገድ አቅርቦ ማወያየት ነው።
አቶ በቀለ ነጋ፥ የኦሮሞ ፌድራላዊ ኮንግሬስ ዋና ጸሃፊ።

በርዕሱ ላይ የተጠናከሩትን ዘገባዎች ከዚህ ያድምጡ፤

የተቃውሞ ሰልፎች በኦሮሚያና በውጭ አገሮች ከተሞች፥ ግጭቶችና አማራጮች
please wait

No media source currently available

0:00 0:16:39 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ
“በኦሮሚያ ግድያና እስራት ይቁም” በዋሽንግተን ዲሲ የተካሄደ ሰልፍ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:24 0:00

XS
SM
MD
LG