በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት አፈናው ተባብሷል- የጥናት ባለሞያዎች


ፊሊክስ ሆርን እና ሃሌሉያ ሉሌ /ከትዊተር እና ከአሶሽየትድ ፕረስ የተገኙ ፎቶዎች/
ፊሊክስ ሆርን እና ሃሌሉያ ሉሌ /ከትዊተር እና ከአሶሽየትድ ፕረስ የተገኙ ፎቶዎች/

ዛሬ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት ቀን ነው። ይህን ቀን ምክንያት በማድረግ “በኢትዮጵያ ያለው የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት ምን ይመስላል?” ስትል ጽዮን ግርማ የሂዩማን ራይትስ ዎች የጥናት ባለሞያ ፍሊክስ ሆርንና የደህንነት ጥናት ተቋም የጥናትና ምርምር ባለሞያ ሃሌሉያ ሉሌን ጠይቃለች። ሁለቱም ባለሞያዎች በኢትዮያ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት እጦት ተባብሷል ይላሉ። ሙሉ ዘገባውን ከዝግጅቱ።

የሂዩማን ራይትስዎች የጥናት ባለሞያ ፍሌክስ ሆርን በኢትዮጵያ የታፈነ ድምፅ አለ ሲል በቅርቡ አንድ ጥናት አቅርቦ ነበር። ለጹሑፉ በግብዓትነት ከተጠቀማቸው ማስረጃዎች መካከል 100 ሰዎችን ማነጋገሩን ገልጿል። በ1997 ዓ.ም ምርጫውን ተከትሎ ከተነሳው ተቃውሞ ቀጥሎ በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ለአምስት ወራት ያህል የተደረገው ተቃውሞ ትልቁ ቢሆንም መረጃው ወደ ውጭ እንዳይወጣና ከውጭ ወደ ውስጥ እንዳየሰራጭ መንግሥት ከፍተኛ አፈና አድርጓል ይላል።

የደህንነት ጥናት ተቋም የጥናትና ምርምር ባለሞያ ሃሌሉያ ሉሌ በበኩሉ በኢትዮጵያ ያለው የፕሬስ ነፃንት ካለፈው ዐሥር ዓመት ወዲህ ያለው ሁኔታ ቢታይ እንኳን የአሁኑ በጣም የባሰ እንደሆነ ይናገራል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ።

በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት አፈናው ተባብሷል- የጥናት ባለሞያዎች
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:14 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG