በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በክትባቶች ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ላይ እየተካሄደ ነው


Immunization Africa
Immunization Africa

“ኢቦላን እንዴት መቆጣጠር እንዳለን እናውቃለን። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ከምዕራብ አፍሪቃ አገሮች ጋር በመሥራት ለሥኬት የበቃ ከፍተኛ ጥረት አድርጓል። ይህ ባይሆን ዓለም አቀፍ ቀውስ ይሆን ይችል ነበር። ዚካን በተመለከተ ግን ሳይንቲስቶች ክትባት ለማግኘት ተግተው እየሰሩ ነው። እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ ጊዜ ሊጠይቅ ይችላል።” ዶ/ር ቶማስ ፍሪዳን የዩናይትድ ስቴትስ የበሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል ዲሬክተር።

ለዚካ ቫይረስ የሚሰጥ ክትባት ለማግኘት እስከ ሁለት ዓመት ሊወስድ እንደሚችል የገለጡት የUS የበሽታዎች መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል CDC ዲሬክተር፤ የባለ ሞያዎች ጥረት ግን መቀጠሉን አስረድተዋል።

ዲሬክተሩ ዶ/ር ቶማስ ፍሪዳን አዲስ አበባ ላይ በመካሄድ ላይ ባለውና በክትባቶች ላይ ባተኮረው የአፍሪቃ የጤና ሚንስትሮች ጉባኤ ላይ ተገኝተዋል።
በክትባቶች ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ ጉባኤ አዲስ አበባ ላይ እየተካሄደ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:44 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG