በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ነጋዴዎች ለቅዳሜ ገበያ ቃጠሎና ንብረት ውድመት ተጠያቂው መንግስት ነው ይላሉ


ጎንደር ቅዳሜ ገበያ ቃጠሎ
ጎንደር ቅዳሜ ገበያ ቃጠሎ

በጎንደር ከተማ በቅዳሜ ገበያ ላይ ለደረሰው ቃጠሎ ንብረት ውድመት ተጠያቂው መንግሥት ነው ሲሉ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነጋዴዎች ተናገሩ። የክልሉ መንግስት እሳቱ የጠፋው ሕዝብና መንግስት ባደረገው ርብርብ ነው ብሏል።

ጎንደር ከተማ ውስጥ በመገበያያ ቦታነት ረጅም ጊዜ እንዳስቆጠረ የሚነገርለትና በተለምዶ “ቅዳሜ ገበያ” ተብሎ የሚጠራው የገበያ ቦታ ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት አደጋ ወደ 420 ሱቆች ሙሉ ለሙሉ መውደማቸው ተገለጸ።

የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ሱቅ የተቃጠለባቸው ነጋዴዎች ሆን ተብሎ የተደረገ ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸው እሳቱን ተቆጣጥሮ ንብረቱን ከውድመት ማትረፍ ያልተቻልው በመንግሥት ታጣቂዎች ተኩስ ምክንያት ነው ይላሉ።

የክልሉ መንግስት ቃል አቀባይ በበኩላቸው እሳቱ በምን እንደተነሳ እንዳልታወቀ ግልጸው ሕዝብና መንግስት ባደረገው ርብርብ እሳቱ ሊጠፋ ችሏል ብለዋል።

ጽዮን ግርማ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው የደምጽ ፋይል ያድምጡ።

ነጋዴዎች ለቅዳሜ ገበያ ቃጠሎና ንብረት ውድመት ተጠያቂው መንግስት ነው ይላሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:11:25 0:00

XS
SM
MD
LG