በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከእስር የተፈቱ ሰዎች ቀጣይ ሕይወት


አዲስ አበባ የሚገኘውና በቅርቡ መዘጋቱ በኢትዮጵያ መንግስት ይፋ የተደረገው ማዕከላዊ እስር ቤት። (©DigitalGlobe 2013 / Source: Google Ear
አዲስ አበባ የሚገኘውና በቅርቡ መዘጋቱ በኢትዮጵያ መንግስት ይፋ የተደረገው ማዕከላዊ እስር ቤት። (©DigitalGlobe 2013 / Source: Google Ear

ከእስር የተለቀቁት ሰዎች መልሰው እንቋቋሙ ምን ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል? ድጋፉንስ ሊሰጣቸው የሚገባው ማነው? በሚሉና በሌሎች ከእስር የተለቀቁ ሰዎችን በሚመለከቱ ጉዳዮች የተደረገ ውይይት።

ኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎችን ሰብዓዊ መብቶችን በመጣስ፣ ሰዎችን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ማሰቃየትና ስብዕናን በሚያዋርድ ሁኔታ በመያዝ በዓለምአቀፍ ተቋማትና በሀገር ውስጥ ተቃዋሚዎች፣ እንዲሁም በመደበኛ ዜጎቿ ስትወቀስ ቆይታለች።

ነገር ግን በቅርቡ መንግሥት እራሱ ያቋቋመው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ይህንኑ የሀገሪቱን የመብቶች ጥሰት ታሪኮች እያረጋገጡ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለእነዚያ ያለፉ ዓመታት የጭካኔና የሥቃይ አድራጎቶች በአደባባይ ይቅርታ እስከመጠየቅ ደርሰዋል። የመንግሥት የሽብር አድራጎትም ብለው ጠርተውታል።

በተጨማሪም ከእስር እየተለቀቁ የሚገኙት እስረኞች ከእነ ጎደለና የተጎዳ አካላቸው ከእስር ቤት እየወጡ በሀገሪቱ ብሔራዊና የክልል ቴሌቭዥን ጭምር ቀርበው እየተናገሩ ነው።

እስረኞችን ስታነጋግር የቆየችው ጽዮን ግርማ - “ከእስር የተለቀቁት ሰዎች መልሰው እንቋቋሙ ምን ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል? ድጋፉንስ ሊሰጣቸው የሚገባው ማነው?” የሚሉና ሌሎች ጭያቄዎችን አንስታ የሕግ ባለሞያና ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች ተመራማሪ አካታ ተከታዩን ዘግባለች።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ)

ከእስር የተፈቱ ሰዎች ቀጣይ ሕይወት
please wait

No media source currently available

0:00 0:20:48 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG