የሶማልያ የምርጫ ሂደት አንድ ሰው አንድ ድምፅ በሚለው አሰራር ለመጠቀም ተስማምተዋል

  • ሰሎሞን ክፍሌ

ፋይል ፎቶ - የሶማልያ ህግ አርቃቂዎች በፓርላማ ጽ/ቤት ሞቃድሹ እ.አ.እ. 2014

የሶማልያ ማዕከላዊ መንግሥት፣ ጎሣን መሠረት አድርጎ መሪዎችን የመምረጡን አሠራር አስወግዶ አንድ ሰው አንድ ድምፅ በሚለው ሂደት ለመተካት ተስማምተዋል።

የሶማልያ ማዕከላዊ መንግሥት እና በከፊል ነፃ የሆነችው የፑንትላንድ ግዛት ባለሥልጣናት፥ ከዘንድሮው ምርጫ በኋላ፥ ጎሣን መሠረት አድርጎ መሪዎችን የመምረጡን አሠራር አስወግደው፥ አንድ ሰው አንድ ድምፅ በሚለው ሂደት ለመተካት ተስማምተዋል።

እርምጃው በሶማልያ ለዓመታት የቆየውን የፖለቲካ አለመረጋጋትና ግጭቶች ሊያስወግድ የሚያስችል አንድ እጅግ ጠቃሚ እርምጃ ሊሆን ይችላል ተብሎ ይገመታል።

ሞሐመድ ዩሱፍ ከናይሮቢ ያደረሰን አጭር ዘገባ አለ። ሰሎሞን ክፍሌ አቅርቦታል ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሶማልያ የምርጫ ሂደት አንድ ሰው አንድ ድምፅ በሚለው አሰራር ለመጠቀም ተስማምተዋል