በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዓለም በጤና ቀውስ ሥጋቶች እየተጨነቀች ነው


ፋይል ፎቶ - የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ማርጋሬት ቻን እ.አ.አ. 2016
ፋይል ፎቶ - የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ማርጋሬት ቻን እ.አ.አ. 2016

ዓለም ከፊቷ በተደቀኑ አደገኛ በሽታዎች ሥጋት እየተዋጠች መሆኗን በመግለፅ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ማርጋሬት ቻን አሳስበዋል፡፡

በመጭ ወራት ይከተላሉ የተባሉ የጤና ሥጋቶችን ለመቋቋም የሚያስችሉ ፈጣን የተግባር እርምጃዎች እንዲወሰዱ የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ማርጋሬት ቻን ጥሪ አሰምተዋል፡፡

ቻን ይህንን የዓለም ማኅበረሰብ የተቀናጀና ፈጣን እንቅስቃሴ የጠየቁት ለአንድ ሣምንት የሚዘልቀው የድርጅታቸው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጉባዔ ከትናንት በስተያ ሰኞ ጄኔቫ ላይ ሲከፈት ነው፡፡

አንድ ሺህ የሚሆኑ ከመላው ዓለም የተወከሉ የጤና ልዑካን እየተሣተፉበት ባሉት በዚህ ጉባዔ ላይ “ላይቤርያ፣ ሲየራ ሌኦን እና ጊኒ ውስጥ የ11 ሺህ ሰው ሕይወት ከቀጠፈው የኢቦላ ድንበር ዘለል ወረርሽኝ ብርቱ ትምህርት ልንወስድ ይገባናል” ሲሉ ቻን አሳስበዋል፡፡

የዓለሙ የጤና ድርጅት ምላሽ ለመስጠት መድረስ ከነበረበት ጊዜ “ዘግይቷል” እየተባለ የሚወቀስ ሲሆን ድርጅቱ ሊወስድ ይገባ የነበረውን ሙሉ የመቆጣጠሪያ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ኢቦላ ተንሠራፍቶ ዓለምን ማስጨነቅ ጀምሮ እንደነበርም ወቃሾችና ተችዎች ይናገራሉ፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዓለም በጤና ቀውስ ሥጋቶች እየተጨነቀች ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:05 0:00

XS
SM
MD
LG