በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የምክር ቤቶች ምርጫና ዓለም አቀፍ አንድምታው


USA Votes 2010
USA Votes 2010

ማክሰኞ ጥቅምት 23, በ50ውም የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች መራጮች ግዛቶቹን የሚያስተዳድሩ ገዢዎች ይመርጣሉ። የአካባቢ ጉዳዮቻቸውን በብሄራዊው ምክር ቤት መድረክ ትኩረት እንዲያገኝ ለሚያደርጉላቸው ፖለቲከኞችም ድምፃቸውን ይሰጣሉ።

የአገሪቱ ልብ ትርታ በነገው የብሄራዊ ሸንጎ ሸንጎ፥ «የትኛው አሸናፊ ይሆናል?» የሚለውን የተከተለ ነው። በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው ምርጫ የሚመለከታቸው መላው የህግ አውጭው ምክር ቤት አባላትና በየ6 ዓመቱ ከሚመረጡት የህግ መወሰኛው ምክር አባላት አንድ ሦሥተኛው በቀጣዩ ምክር ቤቶች የሚኖራቸው ሚና ማክሰኞ ይወሰናል። ውጤቱም የግለሰብ ዕጩዎቹን ብቻ ሳይሆን፤ ከሁለት ዓመት በፊት፥ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2008 በተካሄደው ከፍተኛ ድምፅ በተመረጡት ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ዲሞክራቲክ ፓርቲና በተቀናቃኙ የሪፐሊካን ፓርቲ መካከል የቀጣዩን የፕሬዝዳንቱን አጀንዳዎች ስኬት ጭምር ይወስናል።

XS
SM
MD
LG