በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዚካ ወረርሽን ለማቆም የተጀመረ ዘመቻ


የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር አንተኒ ኮስቴሎ
የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር አንተኒ ኮስቴሎ

በላቲን አሜሪካና በካሬቢያ አገሮች የሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መስሪያ ቤቶች የዚካ ቫይሬስ ወረርሺኝ ለማስቆም ማህበረሰባዊ ዘመቻ ጀምረዋል። የቫይረሱ አስተላላፊ ትንኝ በሃያ አምስት የዓለም አገሮች ዉስጥ በብዙ ሽህዎች የሚገመቱ ዜጎችን እንደነደፈች ይነገራል።

የዚካ ባይረስ በራሱ እምብዛም አሳሳቢ አይደለም። በትንኝዋ መነደፍ ብዙም ሕመም የማያስከትልና ለሕይወትም የማያሰጋ መሆኑ እየተነገረ ነዉ።

ሆኖም ግን ቫይረሱ አዲስ የተወለዱ ሕጻናት ላይ የአካል መጉዋደል እንደሚያደርስ ታዉቋል። በብራዚል ብቻ እስካሁን አራት ሺህ ህጻናት ላይ የአንጎል አካል ጉድለት ተስተዉሏል።

ቫይረሱ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በዓለም ሰለተሰራጨ በመሆኑ የዓለም ጤና ድርጅት አስቸኩዋይ የዓለም ጤና ጠር ሲል አዉጇል።

ለጸነሱ ሴቶች የሚሰጥ ዚካ መከላከያ ክትባት እስካሁን አልተገኘም። ስለዚህ የዓለም ጤና ድርጅት ማህበረሰቦች፣ የጸነሱ ሴቶችን በሽታዉን ከምታስተላልፍ ትንኝ ለመከላከል ዘመቻ እንዲጀምሩ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር አንተኒ ኮስቴሎ (Anthony Costello)ጥሪ አድርጎል። ሊሳ ሽላይን (Lisa Schlein) ከጄኔቫ የላከችዉን ዘገባ ትዝታ በላቸዉ አጠናቅራለች። የድምጽ ፋይሉን በማጫን ያድምጡ።

የዚካ ወረርሽን ለማቆም የተጀመረ ዘመቻ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:59 0:00

XS
SM
MD
LG