ዋሽንግተን ዲሲ —
የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ ተመስገንን ለመጠየቅ ዝዋይ እስር ቤት መመላለስ ከጀመሩ ዘጠኝ ቀናት መቆጠሩን ገልፆ “ተመስገን እዚህ የለም” የሚል ምላሽ ከማግኘት ውጪ ተጨማሪ ምላሽ ማግኘት እንዳልቻሉ ተናግሯል።
የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ ድርጅት ሲ.ፒ. ጄ የምስራቅ አፍሪካ ተጠሪ ሙረቲ ሙቲጋ የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቤተሰብን ስጋት መስማታቸውን ገልፀው ጉዳዩም በጣም እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል።
ጽዮን ግርማ ያጠናቀረችውን ዘገባ ለማድመጥ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ይጫኑ።