ወ/ሮ ዮዲት አምሃ ላለፉት 28 ዓመታት በዚህ በአሜሪካ ሃገር በሴቶች እና ብቸኛ ስደተኛ ህጻናት ላይ ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን በጾታ እኩልነት ዙሪያም ሰፊ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ፡፡ ኮቪድ 19 በከፍተኛ ሁኔታ የአገልግሎት ዘርፉን ማጥቃቱና በዚህም የተነሳ በዘርፉ ውስጥ ያሉ እጅግ ብዙ ሴቶች መቸገራቸውን አንስተው የመፍትሄ አማራጮችን እና የተለያዩ ሴቶችን ያበቃሉ ያሏቸውን እድሎች ጠቁመዋል፡፡
የነገ ተስፋ ሕጻናት ለአዲስ አበባ፤ የተሰኘው መርሃግብር በአ.አ አስተዳደር የህጻናት ቀዳማዊ ልጅነት መርሃግብር በኩል በ 10 ክፍለከተማዎች ከአንድ እስከ ስምንት ዓመት እድሜ ላሉ ሕጻናት የሚያገለግል የመጽሃፍት ማዕከል እና የህጻናት ማቆያ እያዘጋጀ ይገኛል፡፡ ቢሮው በጎፍቃደኞች በዚህ የእድሜ ክልል ላሉ ሕጻናት የሚያገለግሉ መጽሃፍትን እንዲለግሱም ጥሪ አድርጓል፡፡ የመርሃግብሩ አስተባባሪ ዶ/ር ታቦር ገብረመድህን ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ቆይታ አድርገው ነበር፡፡
ከ160 ዓመት በፊት በጉራጌ ዞን እንደኖረች እና ለሴቶች መብት መከበር ትታገል እንደነበር በሚነገርላት በቃቄ ውርድወት ስም የተሰየመው መብቶች እና የዴሞክራሲ እድገት ማሕበር(CARD) የሚያዘጋጀው 'ውርድወት የምርምር መርሃግብር' ወይም ፌሎውሺፕ የመጀመሪያ ምርምር ውጤቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ጥናቱ በየጊዜው በሴቶች የሚደረጉ የጽዋ ፣ ጀማ እና የጸሎት ቡድኖች በሴቷ ስነልቦናዊ እና ኢኮኖሚያ ሕይወት ዙሪያ ያላቸውን ሚና ላይ ያተኮረ ነው፡፡
በሳምንቱ መግቢያ ላይ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ተከብሯል፡፡ በኢትዮጵያም በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍል ያሉ ግጭቶች ለሴቶች እና ህጻናት መፈናቀል፣ ለአካላዊ እና ስነልቦናዊ ጥቃት እንዳጋለጧቸው ይታወቃል፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ዘጋቢዎች ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በማስመልከት ኮቪድ 19 እና ግጭት በሴቶች ላይ ያሳደረውን ጫና ከተለያየ የሃገሪቱ ክፍል አሰባስበው የላኩትን ዘገባ ቆንጂት ታዬ እና ኤደን ገረመው እንደሚከተለው አጠናቅረውታል፡፡
በአውሮፓዊያኑ 2021 ዓ.ም የተባበሩት መንግስታት ተቋማት የቤተሰብ ምጣኔ 2020(ሃያ ሃያ) የዓለም አቀፍ የትብብር እና ተነሳሽነት ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ሪፖርቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ 67 ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ባላቸው ሃገራት ላይ የተሰራ ሲሆን ምንም እንኳን በድሃ ሃገራት ውስጥ ያለው የቤተሰብ ምጣኔ ተጠቃሚነት ቢጨምርም የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ግን የቤተሰብ ምጣኔ እቅዱን በተገቢው መንገድ ለማስኬድ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረ አመላክቷል፡፡
ቤተልሄም ደጀኔ ለወረቀት አምራች ድርጅቶች የሚያገለግል ጥቅል ወይም ፐልፕ ሙሉ ለሙሉ ከግብርና ተረፈ ምርቶች የሚያመርት ዛፍሪ የተሰኘ ተቋም መስራች እና ስራአስኪያጅ ናት፡፡ ከ5 ዓመታት በፊት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ የተመረቀችው ይቺ ወጣት በዋናነት በአካባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረቷን ያደረገች ሲሆን ሙሉ ለሙሉ ከዛፍ ምርት ነጻ የሆነ እና በተጨማሪም ለአነስተኛ ገበሬዎች ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ሊሆን የሚችል ምርት ለማቅረብ ዝግጅቷን ጨርሳለች፡፡
ደራሽ እርዳታ እየተሰጠ ያለበትን ጨምሮ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የተጓዘው አካባቢዎቹ ዘጋቢያችን የተመለከተው ከተከታዩ ዘገባ ያዳምጡ።
እውቁ ተዋናይ እና ጸሐፌ ተውኔት ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ በ84 ዓመታቸው አረፉ። ተስፋዬ ገሰሰ በኢዮጵያ ዘመናዊ የመድረክ ትወናን ካስተዋወቁት ቀዳሚ ተጠሪዎች መካከል እንደነበሩ ይታወቃል። መለስካቸው አመሐ ዘገባ አለው።
ማይካድራ ውስጥ በመቶዎች ሲቪሎች ላይ ጭፍጨፋ ለመካሄዱ ማስረጃ እንዳለው አምነስቲ አስታወቀ።ድርጊቱ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች ስለመፈፀሙ መረጃዎች ያመለክታሉ ሲል ያነጋገራቸውን እማኞች ቃል ጠቅሶ በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል።የትግራይ ክልል በትግራይ ሕዝብ ላይ የተጀመረው ከባድ የዘር ማጥፋት ወረራን ለመቀጠል ሆን ተብሎ የተሰራጨ የሐሰት ዜና ነው ብሎታል። በአካባቢው የነበረ የህወሃት ልዩ ሃይልና ሚሊሻ የፈጸመው ጅምላ ጭፍጨፋ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል:
ድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በአስተዳደሩ ትምህርት ለማስጀመር አራት ዓይነት አማራጮችን ሊጠቀም ማሰቡን አስታወቀ። የአስተዳደሩ ትምሕርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የህጻናትን ደህንነት ባስጠበቀ መልኩ ትምህርት እናስጀምራለን ብለዋል። መግለጫውን የተከታተለው አዲስ ቸኮል ዝርዝር ዘገባ አለው።
በኢትዮጵያ በሕጻናት እና በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል እና በወላጆች ፣ በአሳዳጊዎች ፣ በመምህራን እንዲሁም በአጠቃላይ በኅብረተሰቡ ዘንድ ያለውን ንቃት ለመጨመር የሚያስችል ከለላ የተሰኘ መምሪያ በበጎ ፈቃደኞች ተዘጋጅቶ ለህዝብ ቀርቧል፡፡ ኤደን ገረመው የከለላ ለልጆች መስራች እና አዘጋጅ የተግባቦት ባለሞያ እና አማካሪ የሆነችውን ሰላም ሙሴን አነጋግራ ተከታዩን አሰናድታለች፡፡
ቤኒሻንጉል ጉምዝ ውስጥ 378 ሰዎች፤ ጋምቤላ ውስጥ ደግሞ 645 ሰዎች በኮቪድ 19 መያዛቸውን የክልሎቹ የጤና ቢሮዎች ኃላፊዎች ገልፀዋል።ጋምቤላ ውስጥ ሰባት ሰዎች በኮቪድ 19 ምክንያት መሞታቸው ተነግሯል።
የየመን ሁቲ አማጺያን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ከሀገራቸው ለማስወጣት በከፈቱት ተኩስ በርካታ ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂውማን ራይትስ ዎች ትላንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የተኩስ ጥቃቱን ለማምለጥ ወደ ሳውዲ ድምበር ለመግባት የሞከሩ በርካታ ስደተኞች ላይ የሳውዲ ድምበር ጠባቂ ወታደሮች ተኩስ በመክፈታቸው ተጨማሪ ኢትዮጵያኖች መሞታቸውንም መግለጫው አካቷል።
የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ እና በርሳቸው መዝገብ የተከሰሱ ሃያ ሰዎች በ2 ሚሊዮን ብር ዋስ ተለቅቀዋል። በዋስ መለቀቃቸውን ተከትሎ ዞኑ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እየተመለሰ መሆኑን የዞኑ ነዋሪዎች ለቪኦኤ ገልፀዋል።
እስራኤል እና የተባበሩት የአረብ ኤሚሬቶች ግንኙነታ ለመቀጠል መስማማታቸውን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ ትናንት አስታወቁ።ይህ ስምምነት የአብራሃም ውል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል እስራኤል እ ኤ አ በ 1948 ነጻ ሃገር ሆና ከተመሰረተችበት ጊዜ አንስቶ ከዚህኛው በፊት ከአረቦች ጋር የሰላም ስምምነት ያደረገችው ሁለት ጊዜ ብቻ ነው።
የክልሉ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ እንዳስታወቀው የኮረናቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ተብሎ የይቅርታ መምርያ የሚያሟሉ የህግ ታራሚዎች እንዲፈቱ ተወስኗል::
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መስፋፋት ከጀመረ አንስቶ እስካሁን ባለው ጊዜ እዚያ በስደተኛነት ይኖሩ የነበሩ ከአሥር በላይ ኢትዮጵያዊያን በበሽታው ምክንያት መሞታቸው ተነግሯል።
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በህብረተሰቡ ውስጥ በፈጠረው ፍራቻ ምክንያት የደም ለጋሾች ቁጥር እጅጉን ቀንሷል።ይህም በጤና ተቇማት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን የብሄራዊ ደም ባንክ አገልግሎት አስታውቇል። በተለይ ብስፋት የደምልገሳ ይካሄድባቸው የነበሩት ትምህርት ቤቶች መዘጋትና ከቫይረሱ ጋር ተያይዘው የወጡ መመሪያዎች ለደም ለጋሾችመመናመን አስተዋፅኦ አድርገዋል።
ለኮረና ቫይረስ ተጋልጠው ይሆናል በሚል የተጠረጠሩ ሰዎች የሚወሰደው ናሙና እንዴት ይመረመራል? ውጤቱን ለማወቅስ ስንት ቀን ይወስዳል?
ለኮረና ቫይረስ ተጋልጠዋል በሚል የተጠረጠሩ ሰዎችን ነጥሎ ማቆያ ጣቢያዎች ይዘት ምን ይመስላል? ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ባለሞያ ጠይቀን ያጠናቀርነውን ዘገባ ተከታተሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአቶ ጃዋር መሐመድን ኢትዮጵያዊ ዜግነት ሁኔታን እንዲያረጋግጥ ቀነ ገደብ የተቀመጠለት ሁለተኛ ደብዳቤ ለኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ጻፈ። ኦፌኮ በበኩሉ ጉዳዩ በሕጉ መሠረት እልባት እንዲያገኝ እናደርጋለን ብሏል። (ዝርዝሩን ያዳምጡ)
“ሰብዓዊ መብትትን የሚጥሱ ሰዎች ላይ ለምን እርምጃ ተወሰደ? የሚል ተቃውሞ ማሰማት እጅግ አሳዛኝ ነው” - አቶ ታዬ ደንዳአ
ተጨማሪ ይጫኑ