የአምቦው ወጣት አብደታ ኦላንሳ በምን ምክንያት ሞተ?

  • ቆንጂት ታየ
    ጃለኔ ገመዳ

ፋይል ፎቶ - አምቦ እአአ 2014

ከስድስት ወራት በፊት ከአምቦ ከተማ ተወስዶ አዲስ አበባ ፌዴራል እስር ቤት የነበረ ወጣት አብደታ ኦላንሳ ታሞ በቅዱስ ጳውሎስ አቤት ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ባለፈው ሰኞ ህይወቱ አልፉዋል። ትናንት ረቡዕ የቀብሩ ሥነ ስርዓት በአምቦ ከተማ ተፈጽሙዋል።

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እንደሚሉት ወጣት አብደታ እሥር ቤት ሳለ በደረሰበት ድብደባና ሰቆቃ ራሱን እንደሚያመው ለረጅም ጊዜ ይናገር ነበር።

ወጣቱን ለህልፈት ያበቃው ምክንያት ምንድነው? በህክምና ሲረዳ የነበረበትና በኋላም ያረፈበት ጳውሎስ ሆስፒታል ሥር የሚገኘው የአቤት ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ እና የውስጥ ደዌ ሃኪም ዶክተር ኢስማኤል ሸምሰዲንን ጃለኔ ገመዳ አነጋግራቸዋለች። ከዚህ በታች ያለውን የድምጽ ፋይል በመጫን ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የአምቦው ወጣት አብደታ ኦላንሳ በምን ምክንያት ሞተ?