ገንዘቤ ዲባባ ለ26 ዓመታት ተይዞ የቆየውን የአንድ ማይል የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች

  • ሰሎሞን ክፍሌ

ገንዘቤ ዲባባ በስቶክሆልም - ፋይል ፎቶ

ገንዘቤ ዲባባ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ አዲስ ያስመዘገበችው የዓለም ክብረ ወሰን 4 13 31 ሲሆን ላለፉት 26 ዓመታት ሳይደፈር ከቆየው ጊዜ ላይ አምስት ሴኮንዶች ግድም ላጭታለታለች።

ገንዘቤ ዲባባ በአዳራሽ ውስጥ ሩጫ ውድድር ለ 26 ዓመታት ተይዞ የቆየውን የአንድ ማይል የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች። ባሁኑ ወቅት 5 የዓለም ሬኮርድ ባለቤት ነች።

ገንዘቤ ዲባባ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ አዲስ ያስመዘገበችው የዓለም ክብረ ወሰን 4 13 31 ሲሆን ላለፉት 26 ዓመታት ሳይደፈር ከቆየው ጊዜ ላይ አምስት ሴኮንዶች ግድም ላጭታለታለች።

ገንዘቤ ዲባባ [ፎቶ አሶሽየትድ ፕረስ / AP Photo]

ገንዘቤ በተጨማሪ ሌላ ድል ከሁለት ቀናት በሁዋላ ተጎናጽፋለች። በስፔን ከተማ በሣባዴል ባዳራሽ ውስጥ የ 3 ሺህ ሜትር በታሪክ ፈጣኑን ጊዜ በማጻፍ አጠናቃለች።

በሌላ የአትሌቲክስ ዜና፥ WADA ማለትም የዓለሙ የፀረ-ጉልበት ሰጪ መድሃኒት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ፥ ኬንያን ከ 2016 ቱ የሪኦ ኦሊምፒክ ለማገድ መዘጋጀቱን አስታውቋል። ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ 40 የኬንያ አትሌቶች የጉልበት ሰጪ መድሃኒት ምርመራ አለማለፋቸው ተረጋግጧል።

Your browser doesn’t support HTML5

ገንዘቤ ዲባባ ለ26 ዓመታት ተይዞ የቆየውን የአንድ ማይል የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች