ታጣቂዎች በግብጽ ጥቃት ከፍተው አምስት ፖሊሶች መግደላቸው ታወቀ

  • ቆንጂት ታየ

የቦምብ ጥቃት በጊዛ ከተማ ግብጽ ውስጥ ከተከሰተ በኋላ የፀጥታ አስከባሪ አባሎች የተጎዱትን ሰዎች እየወሰዱ(ፎቶ ሮይተርስ/REUTERS)

ግብጽ እአአ በ2013 ዓ. ም. እስላማዊው ፕሬዚደንት ሞሃማድ ሞርሲ በጦር ሰራዊቱ ከስልጣን ከተወገዱ ወዲህ ታጣቂዎችን ስትታገል ቆይታለች።

በግብጽ ሁከታማ በሆነው የሲናይ ልሳነ ምድር ታጣቂዎች በፍተሻ ኬላ ላይ ተኩስ ከፍተው አምስት ፖሊሶች መግደላቸውን የአገር አስተዳደር ሚኒስቴሩ አስታወቀ።

የቦምብ ጥቃት በጊዛ ግብጽ እአአ 2016

የሲናይ ትልቋ ከተማ በሆነችው ኤል አሪሺም ትናንት ረቡዕ ማታ በደረሰው ጥቃት ሶስት ፖሊሶች መቁሰላቸውን ሚኒስቴሩ አመልክቷል። ለጥቃቱ ሃላፊነት የወሰደ ወገን ግን የለም።

ግብጽ እአአ በ2013 ዓ. ም. እስላማዊው ፕሬዚደንት ሞሃማድ ሞርሲ በጦር ሰራዊቱ ከስልጣን ከተወገዱ ወዲህ ታጣቂዎችን ስትታገል ቆይታለች።

ለሚደርሱት ለአብዛኞቹ ጥቃቶች የእስልምና መንግሥት ብሎ ራሱን የሚጠራው ቡድን ግብረ አበር የሆነ ታጣቂ ቡድን ሃላፊነት ሲወስድ ቆይቷል። የዜና ዘገባውን ለማዳመጥ የድምጽ ፋይሉን ይጫኑ።

Your browser doesn’t support HTML5

ታጣቂዎች በግብጽ ጥቃት ከፍተው አምስት ፖሊሶች መግደላቸው ታወቀ