አዲስ አበባ —
በቅርቡ ወደ ጋምቤላ ክልል በመግባት ሃያ ስምንት ሰዎችን የገደሉትና ሕፃናትን ጠልፈው የወሰዱት ዶ/ር ሪያክ ማቻር ከሚመሩት አማፂያን ጋር ሕብረት የፈጠሩ ሙርሌዎች ናቸው ሲሉ በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ተናገሩ፡፡
አምባሳደሩ ጄምስ ሞርጋን ለአሜሪካ ድምፅ እንዳብራሩት የአሁኑ ጥቃት ከአንድ ዓመት በፊት ከተፈፀመው የተለየ ነው፡፡
ከደቡብ ሱዳን የመጡ የሙርሌ ተወላጆች ዳግም ጥቃት ፈፅመው ሃያ ስምንት ገድለዋል አርባ ስምንት ሕፃናትን አፍነው ወስደዋል፡፡
በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጄምስ ሞርጋን ለዚሕ ተጠያቂው የመንግሥታቸው ተቀናቃኝ ዶ/ር ሪያክ ማቻር መሆናቸውን ነው የሚናገሩት ፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ