ዋሽንግተን ዲሲ —
ዛሬ ጥምቀት ነው። ለተከበራችሁ የእምነቱ ተከታዮችና ለአድማጮቻችንም፣ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ በማለት ከአሜሪካ ድምፅ ራድዮ አፍሪቃ ቀንድ አገልግሎት መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን።
አለው አለው ሳቢሳ፣ አለው ሳቢሳ
ቅዱስ ጊዮርጊስ (ቅዱስ ገብሬል - -) ሲነሳ
አለው አለው ብር ዋንጫ፣ አለው ብር ዋንጫ
የስላሴ መጠጫ -- እያሉ፣ ምእመናን፣ ሴቶች በእልልታ፣ ወንዱ ደግሞ በሆታ ታቦታቱን አጅበው ይጓዛሉ። ይህ፣ ከኢትዮጵያ የጥምቀት አከባበር አንዱና የተለመደው ክፍል ነው።
የጥምቀት አከባበር በኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስትያን
4/11
ከጥቂት ዓመታት በፊት ክዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የቀድሞው ፓትርያርክ አቡነ ፓውሎስ (Patriarch Abuna Paulos) በጥምቀት ሥነ-ስረአት ጊዜ አዲስ አበባ እአአ 2004 እያከበሩ በነበሩበት ወቀት የተነሳ ፎቶ
6/11
Ethiopian worshippers are baptized by a water hose from Patriarch Abuna Paulos, the head of the Ethiopian Orthodox Church during annual Epiphany celebrations called "Timket" in Addis Ababa January 20, 2004.
Previous slide
Next slide
ለመሆኑ ጥምቀት ለአማንያኑ ምን ትርጉም አለው? አዲሱ አበበ ለተለያዩ የእምነቱ ተከታዮች ያቀረበው ጥያቄ ነው። ከዚሁ ጋር፣ "ምን ዓይነት የጥምቀት ትዝታ አለዎ?" በማለትም የሃይማኖቱን ተከታዮች ምእመናን ጠይቋል።
የአንድ ሁለቱ አስተያየት በቀጣዩ ቅንብር ውስጥ ተካቷልና ሙሉውን ዝግጅት በድምጽ ፋይሉ ያገኙታል፣ ፋይሉን በመጫን ያድምጡ።