በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አርሶ አደሮች በዘንድሮውም መኸር የግብአት አቅርቦት ላይ ስጋታቸውን ገለጹ


አርሶ አደሮች በዘንድሮውም መኸር የግብአት አቅርቦት ላይ ስጋታቸውን ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:54 0:00

አርሶ አደሮች በዘንድሮውም መኸር የግብአት አቅርቦት ላይ ስጋታቸውን ገለጹ

በዘንድሮው የመኸር እርሻ በቂ የምርት ግብአቶችን በወቅቱ ላያገኙ እንደሚችሉ ያመለከቱ አርሶ አደሮች፣ በአቅርቦቱ ላይ ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል፡፡

ባለፈው መኸር ያጋጠመውን የአፈር ማዳበሪያ እጥረት ያወሱና ዘንድሮም ሊደገም እንደሚችል የጠቆሙ አንድ የንግድ እና ምጣኔ ሀብት ባለሞያ፣ “ሁኔታው የምርት እጥረትን ያስከትላል፤ ውጤቱም የኑሮ ውድነቱን የበለጠ አስከፊ ያደርገዋል፤” ሲሉ አመልክተዋል።

የግብርና ሚኒስትሩ ግን፣ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትን ጨምሮ አስፈላጊ የምርት ግብአቶችን በጊዜው ለማቅረብ እየተሠራ መሆኑን ለአገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛ በቅርቡ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG