በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ ከለጋሾች የተገኘው ዕርዳታ አነስተኛ መሆኑ ተገለፀ

በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ ምላሽ እስከ አሁን ከለጋሾች የተገኘው ዕርዳታ አነስኛ መሆኑን የብሄራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሺነር አስታወቁ፡፡ ይሔም ሆኖ ክፍተቱን ለመሙላት የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ኮሚሽነሩ ምትኩ ካሣ ለአሜሪካ ድምፅ አስረድተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ ምላሽ እስከ አሁን ከለጋሾች የተገኘው ዕርዳታ አነስኛ መሆኑን የብሄራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሺነር አስታወቁ፡፡ ይሔም ሆኖ ክፍተቱን ለመሙላት የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ኮሚሽነሩ ምትኩ ካሣ ለአሜሪካ ድምፅ አስረድተዋል፡፡

መቶ በመቶ ዕርዳታ ባይገኝም እንኳን ለልማት የተያዘን በጀት ወደ ዕርዳታ በማዞር ሕይወት መታደግ እንደሚቻል ጠቁመዋል፡፡ ኮሚሽነሩ እንዳሉት በአሁነ ሰዓት ግን ይሄንን ለማድረግ የሚያስገድድ ሁኔታ ላይ አልተደረሰም፡፡

የብሄራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ምትኩ ካሣን ያነጋገራቸው እስክንድር ፍሬው ነው፡፡ ከለጋሾች የተገኘው ድጋፍ አነስተኛ መሆኑን ከሚያብራሩበት ይጀምራሉ፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ ከለጋሾች የተገኘው ዕርዳታ አነስተኛ መሆኑ ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:37 0:00

  • 16x9 Image

    እስክንድር ፍሬው

This item is part of

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG