በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከፓሪስ ወደ ካይሮ ያመራ የነበረ የግብፅ አየር መንገድ አውሮፕላን ተከሰከሰ


አራት ሰዓት በሚወስደው በረራ ዛሬ ሓሙስ ግብፅ አየር ክልል እንደገባ ከበረራ መቆጣጠሪያ ራዳር የተሰወረውን አውሮፕላን ስብርባሪ ለማግኘት በሜዲቴራኒያን ባህር ፍለጋ ቀጥሏል።

ስድሳ ስድስት ሰዎች ይዞ ከፓሪስ ወደ ካይሮ በመብረር ላይ የነበረው የግብፅ አየር መንገድ አውሮፕላን የተከሰከሰው ኬቴክኒካዊ ብልሽት ይልቅ በሽብርተኝ ጥቃት ይመስላል ሲሉ የግብፅ የአቪየሺን ሚኒስትር ተናገሩ ።

የግብፅ የአቪየሺን ሚኒስትር
የግብፅ የአቪየሺን ሚኒስትር

አራት ሰዓት በሚወስደው በረራ ዛሬ ሓሙስ ግብፅ አየር ክልል እንደገባ ከበረራ መቆጣጠሪያ ራዳር የተሰወረውን አውሮፕላን ስብርባሪ ለማግኘት በሜዲቴራኒያን ባህር ፍለጋ ቀጥሏል።

አደጋው እንደደረሰ ከግሪክ የወጡ ዘገባዎች እንዳሉት ከሆነ ከአየር የአውሮፕላኑ ስብርባሪ ነው ተብሎ የተጠረጠረ አካል ሳይታይ አልቀረም።

ዩናይትድ ስቴትስ ፒ 3 ኦሪዮን የሚባሉት የረጅም ርቀት ተጉዋዥ አውሮፕላኖች በመስጠት በፍለጋው በመተባበር ላይ መሆኑዋ ታውቁዋል

የዩናይትድ ስቴትስ የውች ጉዳይ ሚኒስትር ጃን ኬሪ ለግብፅ አየር መንገዱ አውሮፕላን ተሳፋሪዎች ቤተሰቦች የሃዘን መግለጫ አስተላልፈዋል።

ከፓሪስ ወደ ካይሮ ያመራ የነበረ የግብፅ አየር መንገድ አውሮፕላን ተከሰከሰ
please wait

No media source currently available

0:00 0:00:40 0:00

ሚስተር ኬሪ ዛሬ ብረሰልስ ውስጥ ከተካፈሉበት የኔቶ የሰሜን አትላንቲክ ሀገሮች ቃል ኪዳን ድርጅት የሚንስትሮች ስብሰባ በኋላ በሰጡት ቃል የአደጋው መነሾ የሽብር ተግባር ይሁን አይሁን በግምት መናገር እንደማይፈልጉ ገልጸዋል።

XS
SM
MD
LG