በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዩክሬይን የአየር ክልሏ ለሩስያ አሮፕላኖች የተከለከለ መሆኑን አስታወቀች


መንገደኞችት የራሻን S7 አየር መንገድ ለመሳፈር የመጨረሻውን መንገድ ከዩክሬይን ጋር በክዬቭ እየተመለከቱ (ፎቶ - አሶሽየትድ ፕረስ/AP Photo)
መንገደኞችት የራሻን S7 አየር መንገድ ለመሳፈር የመጨረሻውን መንገድ ከዩክሬይን ጋር በክዬቭ እየተመለከቱ (ፎቶ - አሶሽየትድ ፕረስ/AP Photo)

የዩክሬይን ጠቅላይ ሚኒስትር አርሰኒ ያትሰንዩክ (Arseniy Yatsenyuk) ዛሬ ይፋ ባደረጉት መግለጫ፣ ሃገሪቷ የአየር ክልሏ ለሩስያ አሮፕላኖች የተከለከለ መሆኑንና የነዳጅ ካምፓኒ ግዥውን እንደምታቆም አስታወቀች።

ዩክሬይን፣ የአየር ክልሏ ለሩስያ አሮፕላኖች የተከለከለ መሆኑንና፣ የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጪ አገር የሚልከው ጋዝፕሮም (Gazprom) ተብሎ የሚጠራው የነዳጅ ካምፓኒ፣ ከእንግዲህ መላኩን እንደሚያቋርጥ በመግለጹ ዩክሬይንም ግዥውን እንደምታቆም አስታወቀች።

አፍቃሬ ምዕራባውያን የሆኑት ጠቅላይ የዩክሬይን ሚኒስትር አርሰኒ ያትሰንዩክ (Arseniy Yatsenyuk) ናቸው ይህን ዛሬ ይፋ ያደረጉት። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ረቡዕ በተካሄደ ስብሰባ ላይ ሲናገሩ፣ እርምጃው የተወሰደው በብሔራዊ ደኅንነት ጉዳይ የተነሳ መሆኑንና ሩስያም ባላት የትንኮሳ ጠባይ ነው ብለዋል።

ጠቅላይ የዩክሬይን ሚኒስትር አርሰኒ ያትሰንዩክ (Arseniy Yatsenyuk) በክዬቭ ካቢኔ ፋይል ፎቶ እአአ 2015.
ጠቅላይ የዩክሬይን ሚኒስትር አርሰኒ ያትሰንዩክ (Arseniy Yatsenyuk) በክዬቭ ካቢኔ ፋይል ፎቶ እአአ 2015.

ባለፈው ወር ዩክሬይን፣ የሩስያ አውሮፕላኖች አገሯ ላይ እንዳያርፉ አግዳ የነበረ ሲሆን፣ ሩስያ ግን የዩክሬይን አሮፕላኖች በክልሏ እንዲበሩ መፍቀዷ አይዘነጋም።

XS
SM
MD
LG