በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ካማሺ ውስጥ በተከፈተ ጥቃት ሰዎች ተገደሉ


ካማሺ ውስጥ በተከፈተ ጥቃት ሰዎች ተገደሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:48 0:00

ካማሺ ውስጥ በተከፈተ ጥቃት ሰዎች ተገደሉ

ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ሶጌ ከተማ ውስጥ ከትናንት በስተያ ቅዳሜ “ታጣቂዎች ሦስት ሰው ገድለው ንብረት አወድመዋል” ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎችና ባለሥልጣን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

ጥቃቱን የከፈቱት የኦሮሞ ነፃነት ጦር ታጣቂዎች እንደሆኑና ሌሎች ሦስት ሰዎችን ማቁሰላቸውን የወረዳው የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞትሌ እምዬ ጠቅሰው “ተጨማሪ የፀጥታ ኃይል በመግባቱ አካባቢው ተረጋግቷል” ብለዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ጦር ቃል አቀባይ ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ “ተገደሉም፣ ቆሰሉም የተባሉት ውጊያ ላይ የነበሩ ወታደሮች ናቸው” ብለዋል።

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምዥጋ ወረዳ ሶጌ ከተማ ውስጥ ከትናንት በስተያ ቅዳሜ (ታህሳስ 20 / 2016 ዓ.ም) ንጋት ላይ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ቁጥራቸውን በውል ያላረጋገጡት ያልታጠቁ ሰዎች መገደላቸውን አቶ ተሰፋለም አመኑ እንደሚባሉና የከተማዪቱ ነዋሪ መሆናቸውን ለቪኦኤ በስልክ ገልፀዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በመንግስት እና ታጣቂዎች መሀከል በተከፈተ ተኩስ ሰዎች ተገደሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:57 0:00

የምዥጋ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሞትሌ እምዬ “ሸኔ ናቸው” ያሏቸው ታጣቂዎች ቅዳሜ ንጋት ላይ እየተኮሱ ወደ ሶጌ ከተማ እንደገቡና ሦስት ሰው ገድለው ሌሎች ሦስት ሰዎችን ማቁሰላቸውን አመልክተዋል። በወቅቱ “በቂ የመንግሥት ኃይል ከተማዪቱ ውስጥ አልነበረም” ብለዋል።

አጥቂዎቹ “ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ የመንግሥት ንብረት አውድመዋል፤ ሁለት ባንኮችን ዘርፈዋል” ብለዋል።

ከጥቃቲ በኋላ መከላከያ መግባቱንና ከተማዪቱ አሁን መረጋጋቷን ገልፀዋል።

በካማሽ ዞን በሎ ጀገንፎይ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች አቤቱታ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:51 0:00

ውንጀላው የቀረበበት የኦሮሞ ነፃነት ጦር ዓለምአቀፍ ቃል አቀባይ መሆናቸውን የሚገልፁት ዩናይትድ ስቴትስ የሚኖሩት ኦዳ ተርቢ ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ ሰጥተዋል "እርምጃ መውሰዳችን እውነት ነው። ሦስት ሰዎች ተገድለዋል ለተባለውና እኛ በሰላማዊ ሰዎች ላይ እንዳተኮርን ተደርጎ የተገለፀው ትክክል አይደለም። እዚያ የተጎዱት የመንግሥት ኃይሎች እንጂ ሰላማዊ ሰዎች አይደሉም። ወደመ የተባለውም ወታደሮች የመንግሥት ንብረት የሥርዓቱ ጦር ንብረት ነው" ብለዋል።

በመንግሥትና በኦሮሞ ነፃነት ጦር መካከል ሲደረግ የነበረው የሰላም ንግግር ያለ ስምምነት ከተበተነ በኋላ በመካከላቸው ውጥረቱ እየጨመረ መምጣቱ ይሰማል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG