በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ ባለቤታቸው እንደታሰሩ ገለጹ


ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ ባለቤታቸው እንደታሰሩ ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:36 0:00

የዐማራ ክልል ልዩ ኀይል አደረጃጀት በሥራ ላይ በነበረበት ወቅት፣ በዋና አዛዥነት ያገለገሉት ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ፣ ባለቤታቸው ወሮ. መነን ኀይለ፣ ትላንት ምሽት፣ ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ ኀይሎች ተወስደው እንደታሰሩ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ገለጹ።

የዐማራ ክልል ልዩ ኀይል አደረጃጀት በሥራ ላይ በነበረበት ወቅት፣ በዋና አዛዥነት ያገለገሉት ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ፣ ባለቤታቸው ወሮ. መነን ኀይለ፣ ትላንት ምሽት፣ ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ ኀይሎች ተወስደው እንደታሰሩ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ገለጹ።

በበነጋው ዛሬ፣ ወሮ. መነን ይገኙበታል ወደተባለው ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ቢሔዱም ሊያገኟቸው እንዳልቻሉ፣ ብርጋዴር ጀነራሉ ተናግረዋል።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ፣ ትላንት በወቅታዊ ኹኔታ ላይ ባወጣው መግለጫ፣ በዐዲስ አበባ ከተማ፣ ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ ጋራ በተያያዘ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ሰዎች እንዳሉ አመልክቷል። ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG