በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ናንሲ ፐሎሲ ታይዋንን እንዳይጎበኙ ቻይና አስጠነቀቀች



የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ
የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ

የቻይና ማስጠንቀቂያ የተሰጠው አፈጉባዔዋ ታይዋንን በሚቀጥለው ወር ለመጎብኘት ማቀዳቸውን ትናንት ካስታወቁ በኋላ ነው፡፡

የፐሎሲ ጉብኘት “የቻይናን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት በከፍተኛ ደረጃ የሚዳፈር ይሆናል” ብለዋል የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዛሆ ሊጃን።

አፈጉባዔዋና የልዑካን ቡድናቸው ኢንዶኔዥያ፣ ጃፓን ማሌዥያና ሲንጋፖርን እንደሚጎበኙና የዩናይትድ ስቴትስ - ኢንዶፓሲፊክ ጠቅላይ ፅህፈት ቤት በሚገኝባት ሃዋኢም አጭር ቆይታ እንደሚያደርጉ ፋይናኒሺያል ታይምስን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

XS
SM
MD
LG