ጠበቃ ፑ ዢኪያንግ የቻይናን ኮሙኒስት ፓርቲና ፖሊሲዎቹን ነቅፎ በማህበራዊ መገናኛ ላይ በማውጣቱ እስከስምንት ዓመት የሚደርስ እስራት ሊፈረድበት ይችላል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
ቻይና ውስጥ የታዋቂው የመብት ተሟዋጋች ጠበቃ ፑ ዢኪያንግ የፍርድ ሂደት በተካሄደበት የቤጂንግ ፍርድ ቤት ደጃፍ ጥቂት ደጋፊዎቹ ተሰባስበው ድጋፋቸውን ገልጸዋል።
የሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋዜጠኞችን ተቃዋሚ ሰልፈኞችንና የውጭ ዲፕሎማቶች ላይ ወከባ ሲያካሂዱ ቢስተዋልም የጠበቃው ደጋፊዎች በስፍራው ተገኝተው ድጋፋቸውን ከመግለጽ ወደኋላ እንዳልላሉ ዜናው ጠቁሟል።
ጠበቃ ፑ ዢኪያንግ የቻይናን ኮሙኒስት ፓርቲና ፖሊሲዎቹን ነቅፎ በማህበራዊ መገናኛ ላይ በማውጣቱ እስከስምንት ዓመት የሚደርስ እስራት ሊፈረድበት ይችላል።