በደቡብ ኢትዮጵያ በኮንሶ በተቀሰቀሰው ግጭት ጋር በተያያዘ ዛሬ አያሌ ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር እየዋሉና ቤቶችም እየተፈተሹ መሆናቸውን ተነገረ።
አዲስ አበባ —
ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ከ10 ቀናት በላይ ቢሆንም በሕይወት፣ በአካል እና በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት ግን በውል አልታወቀም።
ይሁን እና የ16 ሰዎች ሕይወት እንዳለፈ የኮንሶን ሕዝብ ተወካዮች ነን ያሉ የኮሚቴ አባላት ይናገራሉ።
የደቡብ ክልል መንግሥት ቃል-አቀባይ በበኩላቸው ዛሬ አንድም የእስር እርምጃ እንዳልተወሰደ ይናገራሉ።በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች በቃጠላቸውን እና በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑንም ያስረዳሉ።
ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
በኮንሶ አያሌ ሰዎች መታሰራቸውና ቤቶች መፈተሻቸው የሕዝብ ተወካዮች ገለጹ